ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መረቁ

Date:

አዲስ ሪፖርተር – ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ሞ  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ማለዳ በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ በመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አማካኝነት የተገነባውን የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መርቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመረቁት ይኸው ፕሮጀክት በዝናብ ውኃ ላይ የተመሰረተው የአካባቢውን የግብርና ልምድ የመቀየር አላማ እንዳለውና በአከባቢው ያለውን የገፀ ምድር ውኃ ሐብት በመጠቀም የመስኖ ግብርናን ለማቀላጠፍ እቅድ እንዳለው ታውቋል። ፕሮጀክቱ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተከናወነ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማሕበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ፣ ስራ ላይ ሲውል ቢያንስ 9 ሺህ ሄክታር በላይ የእርሻ መሬትን የሚሸፍን መኾኑንና ለአከባቢው አርሶ አደሮች አስተማማኝ የመስኖ አቅርቦት ይሰጣል የሚል እቅድ እንደተያዘለትና ከ20 ሺህ በላይ የአከባቢውን አርሶአደሮች በቀጥታና በተዘዋዋሪ መልኩ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ የመረቁት የወልወል ወንዝን ልማት ፕሮጀክት በአካባቢው የውኃ አስተዳደር ተቋማት እንደሚደራጅለት የተገለፀ ሲኾን ዘላቂነት ያለው የውኃ (መስኖ) አጠቃቀም በመፍጠር መንግስት ለያዘው በምግብ ሉዓላዊነት የማስጠበቅ እቅድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጣል የሚል እምነት የተጣለበት መኾኑን በመረጃው ተጠቅሷል።

ፕሮጀክቱ፣ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚረዳ ከመኾኑ በተጨማሪ በድርቅ የማይበገር ከባቢን ለመፍጠር ያለመ ሲሆን በቆላማ አከባቢዎች በተደጋጋሚ የሚስተዋለውን የውኃ ችግር ፕሮጀክቱ የመቅረፍ አቅም እንዳለው ተገልጿል።

በቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመሩ በርካታ ፕሮጀክቶች እንዳሉ የሚታወቅ ቢሆንም በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ የሚገኘውና ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመረቁት ፕሮጀክት የመስኖ እርሻ ልማት ከዝናብ የተላቀቀ በማድረግ ረገድ ሚናው ከፍተኛ ነው ተብሏል።

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

Egypt’s Red Sea Signal: Opening the Door to a Historic Nile Agreement with Ethiopia

"sources like The National indicating Egypt's conditional openness to...

አብን በሁመራ፣ አዲረመጥ፣ ኮረም ኦፍላ፣ ጠለምት ራያና አላማጣ ሕዝቡ ለክልልም ምርጫም መሳተፍ አለበት አለ

አዲስ ሪፖርተር - "ህዝባችን ለክልሉ ምክርቤት ጭምር ምርጫ መካሄድ...

“ለዓመታት የፖለቲካ መብታቸው ተገፎ ለኖሩ ዜጎች የዲሞክራሲ ጭላንጭል የፈነጠቀ ታሪካዊ እርምጃ” ወልቃይት

አዲስ ሪፖርተር - የወልቃይት ጠገዴ አማራ የማንነትና ወሰን ኮሚቴ...

“ለአራተኛ ጊዜ ተወረናል” ከወሎ ራያ አማራ ማንነት እና ወሰን አስመላሽ ከሚቴ የተሰጠ መግለጫ

አዲስ ሪፖርተር - "መንግሥትም የህዝቡን የማንነት እና የራስ አስተዳደር...