ባንኮች እስከ ህዳር አጋማሽ ድረስ ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ እንዲያጠናቅቁ ታዘዙ

Date:

አዲስ ሪፖርተር ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ በጋራ ባወጡት አዲስ የአተገባበር ሥርዓት መሰረት የፋይናንስ ተቋማት ብሄራዊ ኦፕሬተር በሆነው ኢት-ስዊች በኩል ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ መስራት መጀመራቸው ተገልጿል።

እስካሁን 10 የሚሆኑ የፋይናንስ ተቋማት ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰሩን ሥራ ጨርሰዋል ሲባል ሌሎች ባንኮች በሙከራ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ይህ አሰራር ባንኮች አገልግሎታቸው ቀልጣፋ እንዲሆንና ማዕከላዊ የመረጃ አያያዝ እንዲኖር ያስችላል ብለዋል። አክለውም ትስስሩ ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር ያላቸውን አገልግሎት ያሳልጥላቸዋል፤ ወጪንም እንደሚቆጥብላቸው አመልክተዋል።

የኢት-ስዊች ቺፍ ፖርት ፎልዮ ኦፊሰር (CPO) አቤኔዘር ወንደሰን በበኩላቸው ከዚህ በፊት ደንበኞች አካውንት ሲያወጡ ባንኮች የደንበኛውን መታወቂያ ለማረጋገጥ ሁለት መቶ ብር በአንድ ሰው ክፍያ እንደሚጠበቅባቸው ለቲክቫህ ከተናገሩት ለመረዳት ተችሏል።

በአዲሱ አሰራር ባንኮች ስንት እንደሚከፍሉ ተመን ባይወጣላቸውም ክፍያው ሲወሰን ከሀምሳ ብር እንደማይበልጥ አስታወቀዋል። ይህም ባንኮችን ከበርካታ ወጪ እንደሚያድናቸው ተናግረዋል። አቶ አቤኔዘር ባንኮች እስከ ህዳር አጋማሽ ድረስ ጥምረት አድርገው መጨረስ እንዳለባቸውም አታወቀዋል።

በአሰራሩ ባንኮቹ ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር በቀጥታ ትስስር አይኖራቸውም። በጥምረቱ ትስስር የሚኖራቸው በኢት-ስዊች በኩል ነው።

ኢት-ስዊች ሁሉንም ባንኮች ያስተሳሰረ ስለሆነ ብሔራዊ መታወቂያ ከኢት-ስዊች ጋር በመቀናጀት ሁሉንም ባንኮች በአንድ ጊዜ ማግኘት ይችላል።

የባንክ አካውንት ሲከፈት ባንኮች የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥሩን ወደ ኢትስዊች ልከው ኢት-ስዊች ባንኩ ስለደንበኛው የሚያስፈልገውን መረጃ (KYC) ከብሔራዊ መታወቂያ ተቀብሎ ለባንኮቹ መልሶ ይልካል።

የብሔራዊ መታወቂያ የጣት አሻራን በክፍያ ወቅት እንደ ይለፍ ቃልም መጠቀም እንዲቻል አሁን ላይ የተጀመሩት ትስስሮች እንደሚያግዙም ተጠቅሷል።

ኢት-ስዊች የፋይናንስ ሪፖርቱን በቅርቡ ሲያቀርብ በባለፈው በጀት ዓመት፥ ጠቅላላ ገቢው 2.2 ቢሊዮን ብር መሆኑን ጠቅሶ ከታክስ በፊት 1.42 ቢሊዮን ብር ማትረፉንና ይህም ካለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ34% ጭማሪ ማሳየቱን ማስታወቁ አይዘነጋም።

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/profile.php?id=61577410241403
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter11
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ኃይሌ ገብረስላሴ “አረቄን እጠቀም ነበር” በማለቱ ዕግድ ተጣለበት፤ እግዱ ለዓለም ዓቀፍ ተቋማትና ማህበራት ተበትኗል

አዲስ ሪፖርተር - አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ አረቄን ከዶፒንግ ጋር...

“የኢትዮጵያዊያ መከራ የሆነውን ትህነግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከኢትዮጵያና ትግራይ ምድር መንቀል ዋና ዓላማችን ነው”

አዲስ ሪፖርተር - እስካሁን በመላው ኢትዮጵያ ለተፈጠሩ ምስቅልቅሎች፣ በትግራይ...

የአማራ ክልል የወሲባዊ ጥቃት አሳስቧል፤ “በማንና እንዴት ይፈጸማል? ለሚለው በጥናት የተረጋገጠ መረጃ የለም” ጤና ቢሮ  

አዲስ ሪፖርተር - በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ባለው ጦርነትና...

በሻዕቢያና ህወሃት መካከል አለመተማመኑ ሰፍቷል፤ የሚታወቁ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ከእነ ሞንጆሪኖ ቡድን እየወጡ ነው

ስጋት ትልቁ ምክንያት ነው። ሻዕቢያ በተግባር የተፈተሸ ከሃጂ በመሆኑ...