አዲስ ሪፕርተር – በሩዋንዳ የሚደገፈው M23 ታጣቂ ቡድን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እያደረሰ ባለው ጥቃት የኮንጎው ፕሬዚዳት ፌሊክስ ኪሲኬዲ የሩዋንዳ መንግስትን ከሰዋል።
እየተባባሰ በመጣው የሁለቱን ሀገራት ውጥረት አስመልክቶ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ መንግስት ሩዋንዳ ከሳምንት በፊት በአሜሪካ የተፈፀመውን የዋሽንግተን ስምምነት ጥሳለች በማለት ክስ አቅርቧል።
የኮንጎ መንግስት ክሱን ያቀረበው የቡሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሴምበር 2 ላይ የሩዋንዳ ወታደሮች የቡሩንዲ ግዛትን መምታታቸውንና እና በኮንጎ የሚገኘውን ወታደራዊ ቦታ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ካሳወቁ በኋላ ነው።
በዚህም መሰረት የቡሩንዲ ወታደሮች በሩዋንዳ የሚታገዘውን የM23ን ጨምሮ የታጠቁ ቡድኖችን ለመዋጋት በተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በዲሞክራቲክ ኮንጎ ተሰማርተዋል።
ከዚህ ቀደም የሩዋንዳ እና የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተሮች በዋሽንግተን የሰላም ስምምነት መፈራረማቸው የሚታወስ ሲሆን በስምምነቱም ሩዋንዳ ወታደሮቿን እንድታስወጣ ፣ የM23 ቡድንን መደገፍ እንድታቆም እና ትጥቅ እንድታስፈታ የሚያዝ ውል ያካትታል።
ሆኖም እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ የM23 ታጣቂዎች ስምምነቱን በመጣስ በኮንጎ ሁለት የደቡብ ኪቩ ግዛት ከተማዎችን መቆጣጠረራቸውንና ጦራቸውን ወደ ኡቪራ ከተማ ማዘዋወራቸው ተገልፇል።
የድምበር ከተማ የሆነችው ኡቪራ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮነጎ ስር የቀረች ብቸኛዋ የደቡብ ኪቩ ግዛትም ሆናለች።
ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/addisreporternews/
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter11
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393






