የኮር፣ የአርሚ አዛዦችና የትህነግ ስራ አስፈጻሚዎች በታደሰ ወረደ መኖሪያ ቤት መሽገዋል፤

Date:

አዲስ ሪፖርተር – በትግራይ ተፈጥሯል የሚባለው የአመራሮች ልዩነት ተከትሎ የትህነግ ስራ አስፈጻሚ፣ የኮርና አርሚ አዛዦች በጊዜያዊ አስተዳደሩ መሪ ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ የግል መኖሪያ ቤት የጀመሩት ስብሰባ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። ዶክተር ደብረጽዮን “የት ናቸው” የሚል ጥያቄም በርክቷል።

የክልሉ የጸጥታ ኃላፊ ፍስሃ ማንጁስ እንደጠሩት የተነገረለት ይህ ስብሰባ በታደሰ ወረደ መኖሪያ ቤት እየተካሄደ ከመገለጹ ውጭ ስለ ስብሰባው አጀንዳና የተደረሰበት ውሳኔ የተባለ ነገር የለም።

ትህነግ ከተከፈለ በሁዋላ “የጽንፈኛ ኃይል” የሚባለው ቡድን ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደን “አትሰማንም፣የምትወስነው ሳታማክረን ነው፣ለፌደራል መንግስት ትታዘዛለህ፣ ከኤርትራ ጋር የተጀመረውን ጽምዶ አትደግፍም” የሚሉና ተመሳሳይ አቤቱታ እንደሚቀርብባቸው በተለያዩ አግባቦች እንደሚደመጥ የሚታወቅ ነው።

በዚህ መነሻ ይሁን በሌላ ቁልፍ ጉዳይ ባይታወቅም ካለፈ ረቡዕ ጀምሮ የክልሉ የጸጥታ ኃላፊ ጠሩት የተባለው ስብሰባ ይህ ዜና እስከታተመ ድረስ በጄኔራሉ መኖሪያ ቤት እየተደረገ ነው። የትግራይ የአዲስ ሪፖርተር ተባባሪ በምስል አስደግፎ እንዳለው፣ ባለስልጣናቱ ወደ ጄኔራሉ የግል መኖሪያ ሲገቡ በርካታ የአይን ምስክሮች አይተዋል። ተሽከርካሪዎቻቸውን ፎቶ በማንሳት አጋርተዋል።

በሌላ ዜና የዚሁ የታገደውና ሕገወጥ የተባለው ትህነግ ሊቀመንበር ዶክተር ደብረጽዮን መሰወራቸው እየተወራ ነው። ከሶስት ሳምንት በፊት በኤርትራ በኩል ዱባይ ከርመው የተመለሱት ዶክተር ደብረጽዮን፣ መታመማቸውን የሚናገሩም አሉ።

ለእሳቸው ቅርብ የሆኑ ሰዎች የሚጋነን ባይሆንም መጠነኛ የጤና መታወክ ገጥሟቸው እንደነበርና እንደተሻላሸው ለአዲስ ሪፖርተር ተባባሪ ነግረዋል። ይሁን እንጂ ህመማቸው ከባድ እንዳልሆነ ቢገለጽም አፅቡ ከተማ በተደረገው የልደት በዓል ላይ አልተገኙም። በግል ለወትሮው እንደሚያደርጉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክትም አላስተላለፉም።

ተባባሪያችን እንዳለው ታደሰ ወረደ የ”እንኳን አደረሳችሁ” መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እሳቸው ከወትሮው በተለየ ዝምታን መምረጣቸው የጤናቸው ሁኔታ ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ እንደሆነ በርካቶች እየተነጋገሩ ነው። በሌላ በኩል ግን ተመልሰው ወደ ውጭ መውጣታቸውን የሚናገሩ አሉ።

ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/addisreporternews/
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

“አሳጋቾቹን ካህናት ስም ዝርዝር ይፋ እናደርጋለን”

አዲስ ሪፖርተር - የወረታ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ...

ዩኒቨርሲቲዎች እንደ ነፃ የሃሳብ ሪፐብሊክ፣ የሁምቦልድት ፍልስፍና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሪፎርም እይታ

ቢልዱንግ እና የሃሳብ ትውልድ እሳቤዎች ሲቀናጁ ምሁራን የቆዩ የትርክት...

የኤርትራ አፋር ተቃዋሚ ድርጅቶች ግንባር ፈጠሩ፤ “ስምምነቱ ለሻዕቢያ አስደንጋጭ መርዶ ነው” አቶ አብዲ ሼኽ መሐመድ

አዲስ ሪፓርተር - በኤርትራ የሚንቀሳቀሱት ሁለት የአፋር ተቃዋሚ ድርጅቶች...