ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የአክሲዮን ዝውውሮች እንዲቆጣጠር ስልጣን የሚሰጠውን ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱን ተሰማ

Date:

አዲስ ሪፖርተር – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከባንኮች ከፍተኛ ባለአክስዮኖችን ከመቆጣጠር አንስቶ እሰከ ማገድ የሚያስችል ሰልጣን የሚሰጠው ረቂቅ መመርያ መሰናዳቱን የተገለፀ ሲኾን ረቂቅ መመርያው ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላትን ለመከታተል እንዲያስችለው የሚረዳ መኾኑን ተገልጿል።

ብሔራዊ ባንክ ያዘጋጀው ረቂቅ መመርያ በዋነኝነት ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላትና ግለሰቦች የገንዘባቸውን ምንጭ እንዲያሳውቁ የሚያስገድድ ስልጣን የሚሰጥ መኾኑንና የተገለፀ ሲኾን አጠቃላይ የፋይናንስ ዘርፉን ጤና ለመጠበቅ ያለመ ነው ተብሏል።

ባንኩ መመሪያውን ለማውጣት የተገደደበት ምክንያት ሲገልፅም በባንኮች ውስጥ የሚኖሩ የአክሲዮን ዝውውሮች ግልፅና ድርሻቸውን በዓለማቀፍ ደረጃ ያለውን የድርሻ መስፈርቶችን ባሟላ መልኩ መካሄዱን ለማረጋገጥና የባንክ ስራ የመጠበቅ ኃላፊነቱ እንዲወጣ የሚረዳው መኾኑን ገልጿል

በቀጣይም ረቂቅ መመሪያውን ለባለድርሻ አካላት እንዲወያዩበት ባንኩ ግብዣ እንደሚያደርግና አስተያየቶችን መስማት እንደሚፈልግ የተገለፀ ቢሆንም በተዘጋጀው በረቂቅ መምርያ ሐሳባቸውን እንዲሰጡ በሚጋበዙት አካላት ዙርያ ባንኩ ያለው ነገር የለም።

በመጀመሪያ ዙር ረቂቅ መመርያው ላይ የሚሰጡ ጠቃሚ አስተያየቶችን ተቀብሎ ለመመርያው ግብአትነት ለማዋል ዝግጁ መኾኑንና ረቂቅ መመርያው በቅርቡ በምክር ቤት የፀደቀው የባንክ ስራ አዋጅን አቅም የሚሰጡ ነጥቦች የተካተቱበት መኾኑንም ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል ።

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

የአዲስ አበባ ሕዝብ የእናት ሀገር ጥሪ ተሳትፎና ኮሎኔል መንግሥቱ

የእናት አገር ጥሪ ከተደረገ በኋላ መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ...

ቢሾፍቱ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ፤ ኢትዮጵያን ወደ መፃኤ ዘመን የሚያሻግር የሎጂስቲክስ አብዮት

ኢትዮጵያ ከቢሾፍቱ ሰማይ ስር የኢኮኖሚና የሎጂስቲክስ ካርታዋን እንደገና ለመሳል...

“ጥርስ የሌለው ውሻ” የሆነው የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የዓለም መፃኢ እጣፈንታ

አዲስ ሪፖርተር - ፕሬዛዳንት ትራምፕ አሜሪካን ከተባበሩት መንግስታት ደርጅት...

በዘመነ ትራምፕ ጫና ውስጥ የወደቀችው ሶማሊያ እና ለሶማሌ ላንድ ተስፋን ያለመለመው አዋጅ

አዲስ ሪፓርተር - ከሶማሌላንድ የሉዓላዊነት ጥያቄ እና ከእስራኤል እውቅና...