ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የአክሲዮን ዝውውሮች እንዲቆጣጠር ስልጣን የሚሰጠውን ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱን ተሰማ

Date:

አዲስ ሪፖርተር – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከባንኮች ከፍተኛ ባለአክስዮኖችን ከመቆጣጠር አንስቶ እሰከ ማገድ የሚያስችል ሰልጣን የሚሰጠው ረቂቅ መመርያ መሰናዳቱን የተገለፀ ሲኾን ረቂቅ መመርያው ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላትን ለመከታተል እንዲያስችለው የሚረዳ መኾኑን ተገልጿል።

ብሔራዊ ባንክ ያዘጋጀው ረቂቅ መመርያ በዋነኝነት ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላትና ግለሰቦች የገንዘባቸውን ምንጭ እንዲያሳውቁ የሚያስገድድ ስልጣን የሚሰጥ መኾኑንና የተገለፀ ሲኾን አጠቃላይ የፋይናንስ ዘርፉን ጤና ለመጠበቅ ያለመ ነው ተብሏል።

ባንኩ መመሪያውን ለማውጣት የተገደደበት ምክንያት ሲገልፅም በባንኮች ውስጥ የሚኖሩ የአክሲዮን ዝውውሮች ግልፅና ድርሻቸውን በዓለማቀፍ ደረጃ ያለውን የድርሻ መስፈርቶችን ባሟላ መልኩ መካሄዱን ለማረጋገጥና የባንክ ስራ የመጠበቅ ኃላፊነቱ እንዲወጣ የሚረዳው መኾኑን ገልጿል

በቀጣይም ረቂቅ መመሪያውን ለባለድርሻ አካላት እንዲወያዩበት ባንኩ ግብዣ እንደሚያደርግና አስተያየቶችን መስማት እንደሚፈልግ የተገለፀ ቢሆንም በተዘጋጀው በረቂቅ መምርያ ሐሳባቸውን እንዲሰጡ በሚጋበዙት አካላት ዙርያ ባንኩ ያለው ነገር የለም።

በመጀመሪያ ዙር ረቂቅ መመርያው ላይ የሚሰጡ ጠቃሚ አስተያየቶችን ተቀብሎ ለመመርያው ግብአትነት ለማዋል ዝግጁ መኾኑንና ረቂቅ መመርያው በቅርቡ በምክር ቤት የፀደቀው የባንክ ስራ አዋጅን አቅም የሚሰጡ ነጥቦች የተካተቱበት መኾኑንም ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል ።

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ትህነግና ሻዕቢያ በጋራ የተቃውሞ መግለጫ አወጡ፤ “ኢትዮጵያ የባህር በር እንዲኖራት አትፈቅድም”

አዲስ ሪፖርተር - በመጥረቢያው ብረትና በእንጨቱ እጀታ የተሳሉት ሻዕቢያና...

በኩርሙክ ግንባር የቀጠለው ጦርነት የአርሚ 70 ተዋጊዎችም ከባድ ጉዳት ድርሶባቸዋል

አዲስ ሪፖርተር | አዲስ አበባ/ካርቱም | ሐምሌ 9 ቀን...

“ወደ ጦርነት መመለስ የለም፤ በስቃይ ፊት ዝምታ አይኖርም፤ የትግራይ ሕዝብ ሥቃይ ሊቆም ይገባል…”

"ይህ የአቋም መግለጫ የጋራ ጥሪያችን ነዉ፤ ወደ ጦርነት መመለስ...