በኢትዮጵያ የወተት ምርት ጥራት አሳሳቢ በመሆኑ ባለስልጣኑ ቁጥጥሩን ሊያጠብቅ ነው

Date:

አዲስ ሪፖረተር – በኢትዮጵያ ለማኅበረሰቡ የሚቀርብ ብዙ መጠን ያለው የወተት ምርት ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ ለሽያጭ የሚቀርብ አምስት በመቶ ብቻ የሚሆነው የወተት አቅርቦት ጥራቱ የጠበቀ መሆኑን የኢትዮጵያ ምግብና መድሐኒት ባለሥልጣን ለአዲስ ሪፖርተር አስታውቋል፡፡

በባለስልጣን መስሪያ ቤት የእንሰሳት ተዋፅዖና አልሚ ምግቦች ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን ለአዲስ ሪፖርተር እንደተናገሩት፤ በሀገሪቱ አጠቃላይ የወተት ምርት አቅርቦት ላይ የጥራት ችግር መኖሩን ተናግረዋል።

ማንኛውም ሰው እንደፈለገ ወተት እያዞረ መሸጥ እንደማይችል፣ ይህን የመረዳትና የማክበር የግንዛቤ ጉድለት በማሕበረሰቡ ዘንድ መኖሩን የገለጹት ኃላፊው፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የወተት ምርትና ሽያጭ ከሚያስፈልገው ከፍተኛ ጥንቃቄ አንፃር በጀሪካንና በሌሎችም ባልተፈቀዱ ዕቃዎች ማጓጓዝ ጥራቱን ከማጓደል ባሻገር ለበሽታ አምጪ ተዋህስያን የሚያጋልጥ መሆኑን አስረድተዋል። አክለውም፤ “ዘርፉ ያላደገ በመሆኑ የሚስተዋሉ የጥራት ችግሮችን ሙሉ ለሙሉ ለመቅረፍ አልተቻለም” ብለዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በወተት ምርቶች በተለይም በባህላዊ መንገድ ለሕብረተሰቡ የሚቀርቡ ምርቶች ከፍተኛ ጥንቃቄን የሚሹ በመሆናቸው፤ ወተት አቅራቢዎች በቂ ስልጠናዎችን በመውሰድ ዘመናዊ አሰራሮችን  ሊከተሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ለዚህም በዋናነት ከሚስተዋሉ ችግሮች አንጻር የመኖ በበቂ ሁኔታ አለመቅረብ እና የእንሰሳት አያያዝ ተጠቃሽ መሆኑን አስረድተዋል። ይህ ማለት ሙሉ ለሙሉ ጥራት የጎደላቸዉ የወተት ምርቶች ገበያ ላይ አሉ ማለት እንዳልሆነ እና ጥራት ያላቸው የወተት ምርቶች ስለመኖራቸው አንስተዋል።

በባለሥልጣኑ በኩል የተጀመሩ የቁጥጥር ሥራዎችን በአዲስ አበባ እና በሌሎች ክልሎችም ተጠናክረው እንደሚሰሩም ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል። የዴስክ ኃላፊው አክለውም ባለሥልጣኑ የወተት ጥራትን ለማስጠበቅ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ ሕጋዊ ሂደቱን በተመለከተ ለማሕበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል።

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

Egypt’s Red Sea Signal: Opening the Door to a Historic Nile Agreement with Ethiopia

"sources like The National indicating Egypt's conditional openness to...

አብን በሁመራ፣ አዲረመጥ፣ ኮረም ኦፍላ፣ ጠለምት ራያና አላማጣ ሕዝቡ ለክልልም ምርጫም መሳተፍ አለበት አለ

አዲስ ሪፖርተር - "ህዝባችን ለክልሉ ምክርቤት ጭምር ምርጫ መካሄድ...

“ለዓመታት የፖለቲካ መብታቸው ተገፎ ለኖሩ ዜጎች የዲሞክራሲ ጭላንጭል የፈነጠቀ ታሪካዊ እርምጃ” ወልቃይት

አዲስ ሪፖርተር - የወልቃይት ጠገዴ አማራ የማንነትና ወሰን ኮሚቴ...

“ለአራተኛ ጊዜ ተወረናል” ከወሎ ራያ አማራ ማንነት እና ወሰን አስመላሽ ከሚቴ የተሰጠ መግለጫ

አዲስ ሪፖርተር - "መንግሥትም የህዝቡን የማንነት እና የራስ አስተዳደር...