“በሰሜን ሸዋ በስም የሚታወቁ የፋኖ አመራሮች፣ አጃቢዎችና ከ60 በላይ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል”

Date:

አዲስ ሪፖርተር – ከተለያዩ የፋኖ አደረጃጀቶች አንዱ ከሆነው የመከታው ቡድን በተገኘ መረጃ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ። በድንገት በተወሰደ እርምጃ አመራሮችን ጨምሮ ታጣቂዎች በገደላቸው ታውቋል።

ከአካባቢው የጸጥታ ኃይሎች የተገኘው መረጃ እንደሚያመልክተው ድንገተኛ እርምጃው የተወሰደው ሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ኩሬ በረት ቀበሌ እቧይ ግድ የተባለ ቦታ ነው።

“ድንገተኛ” የተባለው ኦፕሬሽን የተከናወነው ከመከታው ቡድን በተገኘ መረጃ እንደሆነ ዜናውን ያሰራጩት አመልክተዋል። መከታው ማሞ በደሳለኝ ሲያስብ በሚመራውን የሸዋ ቡድን ላይ ጥቃት ፈፅሞና በርካቶችን አስሮ እንደነበር ያስታወሰው ዜናው፣ መረጃው የተገኘው ከመከታው ቡድን እንደሆነ ቢገልጽም ለተመሳሳይ ኦፕሬሽን ሲባል ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።

እርምጃ የተወሰደባቸውን አመራሮች ስም፣ ማዕረግና ልዩ የስራ ድርሻ ጠቅሶ ይፋ የሆነውን መረጃ አስመልክቶ ይህ እስከተዘገበ ድረስ ማስተባበያ አልተሰማም።
እንደ መረጃው እርምጃ ተወሰደባቸው የተባሉት አመራሮች

1 አጌጠ የሸዋ እዝ ሎጂስቲክስ ኃላፊ
2 አብረሐም የእስረኛ አስተዳደር
3 ሀምሳ አለቃ ታዬ ብርሐኑ የአስቻለው ደሴ ክ/ጦ ዘመቻ ኃላፊ
4 ይበልጣል ማሩ የራምቦ ክ/ጦ ወታደራዊ አዛዥ
5 ተስፋዬ መካሻ የደሳለኝ ሲያስብሸዋ ምክትል አዛዥ እና ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ
6 መቶ አለቃ ልመነው ዘውዴ የደሳለኝ ቡድን ም/ል አዛዥ
7 ዳዊት ቀፀላ የደሳለኝ ቡድን ፖለቲካ ዝርፍ ኃላፊ
8 አብረሐም ብርሌ የደሳለኝ ቡድን ወታደራዊ አዛዥ
9 የኮ/ል ማን ነገረው መለሰ ሶስት ታማኝ አጃቢዎችን ጨምሮ ከ60 በላይ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተመልክቷል። ተመሳሳይ ኦፕሬሽኖች በተለያዩ አካባቢዎች እንደሚደረጉም ለማወቅ ተችሏል።

ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/addisreporternews/
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

Egypt’s Red Sea Signal: Opening the Door to a Historic Nile Agreement with Ethiopia

"sources like The National indicating Egypt's conditional openness to...

አብን በሁመራ፣ አዲረመጥ፣ ኮረም ኦፍላ፣ ጠለምት ራያና አላማጣ ሕዝቡ ለክልልም ምርጫም መሳተፍ አለበት አለ

አዲስ ሪፖርተር - "ህዝባችን ለክልሉ ምክርቤት ጭምር ምርጫ መካሄድ...

“ለዓመታት የፖለቲካ መብታቸው ተገፎ ለኖሩ ዜጎች የዲሞክራሲ ጭላንጭል የፈነጠቀ ታሪካዊ እርምጃ” ወልቃይት

አዲስ ሪፖርተር - የወልቃይት ጠገዴ አማራ የማንነትና ወሰን ኮሚቴ...

“ለአራተኛ ጊዜ ተወረናል” ከወሎ ራያ አማራ ማንነት እና ወሰን አስመላሽ ከሚቴ የተሰጠ መግለጫ

አዲስ ሪፖርተር - "መንግሥትም የህዝቡን የማንነት እና የራስ አስተዳደር...