“በሰሜን ሸዋ በስም የሚታወቁ የፋኖ አመራሮች፣ አጃቢዎችና ከ60 በላይ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል”

Date:

አዲስ ሪፖርተር – ከተለያዩ የፋኖ አደረጃጀቶች አንዱ ከሆነው የመከታው ቡድን በተገኘ መረጃ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ። በድንገት በተወሰደ እርምጃ አመራሮችን ጨምሮ ታጣቂዎች በገደላቸው ታውቋል።

ከአካባቢው የጸጥታ ኃይሎች የተገኘው መረጃ እንደሚያመልክተው ድንገተኛ እርምጃው የተወሰደው ሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ኩሬ በረት ቀበሌ እቧይ ግድ የተባለ ቦታ ነው።

“ድንገተኛ” የተባለው ኦፕሬሽን የተከናወነው ከመከታው ቡድን በተገኘ መረጃ እንደሆነ ዜናውን ያሰራጩት አመልክተዋል። መከታው ማሞ በደሳለኝ ሲያስብ በሚመራውን የሸዋ ቡድን ላይ ጥቃት ፈፅሞና በርካቶችን አስሮ እንደነበር ያስታወሰው ዜናው፣ መረጃው የተገኘው ከመከታው ቡድን እንደሆነ ቢገልጽም ለተመሳሳይ ኦፕሬሽን ሲባል ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።

እርምጃ የተወሰደባቸውን አመራሮች ስም፣ ማዕረግና ልዩ የስራ ድርሻ ጠቅሶ ይፋ የሆነውን መረጃ አስመልክቶ ይህ እስከተዘገበ ድረስ ማስተባበያ አልተሰማም።
እንደ መረጃው እርምጃ ተወሰደባቸው የተባሉት አመራሮች

1 አጌጠ የሸዋ እዝ ሎጂስቲክስ ኃላፊ
2 አብረሐም የእስረኛ አስተዳደር
3 ሀምሳ አለቃ ታዬ ብርሐኑ የአስቻለው ደሴ ክ/ጦ ዘመቻ ኃላፊ
4 ይበልጣል ማሩ የራምቦ ክ/ጦ ወታደራዊ አዛዥ
5 ተስፋዬ መካሻ የደሳለኝ ሲያስብሸዋ ምክትል አዛዥ እና ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ
6 መቶ አለቃ ልመነው ዘውዴ የደሳለኝ ቡድን ም/ል አዛዥ
7 ዳዊት ቀፀላ የደሳለኝ ቡድን ፖለቲካ ዝርፍ ኃላፊ
8 አብረሐም ብርሌ የደሳለኝ ቡድን ወታደራዊ አዛዥ
9 የኮ/ል ማን ነገረው መለሰ ሶስት ታማኝ አጃቢዎችን ጨምሮ ከ60 በላይ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተመልክቷል። ተመሳሳይ ኦፕሬሽኖች በተለያዩ አካባቢዎች እንደሚደረጉም ለማወቅ ተችሏል።

ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/addisreporternews/
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

አሜሪካና ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ ምን እያሰቡ ነው? “አሜሪካ የኢትዮጵያን የባህር ፍላጎት ማሳካት ህልውናዋ ነው”

ኢትዮጵያ የቀጥታ የባህር ዳርቻ ባይኖራትም፣ በወታደራዊ አቅሟ እና የባህር...

“የአሜሪካና ኢትዮጵያ ወዳጅነት አደገኛ ነው፤ ከማን ጋር እንደምንዋጋ አልገባንም፤አሳልፋ ልትሰጠን ትችላለች”

አዲስ ሪፖርተር - በአገር ቤት ሕዝባዊ አመጽ ለማነሳሳት የተደራጀው...

ኤርትራ ለህወሃት መሪዎች የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት የመስጠት ስምምነት አገደች

አዲስ ሪፖርተር - የኤርትራ መንግስት ለህወሃት አመራሮችና ከፈተኛ ወታደራዊ...