የወልቃይት ጠገዴ የማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ በምርጫ ቦርድ እና በስምረት ክርክርጣልቃ ለመግባት አመለከተ

Date:

አዲስ ሪፖርተር – የወልቃይት ጠገዴ አማራ የማንነት እና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ፣ በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ እና በዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) መካከል በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየተካሄደ ባለው የሕግ ክርክር ውስጥ፣ “መብትና ጥቅሜን ይነካል” በማለት የጣልቃ ገብነት አቤቱታ አቅርቧል።

ፍርድ ቤቱ የኮሚቴውን አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለየካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል።

ክርክሩ የተጀመረው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የካቲት 16 ቀን 2018 ዓ.ም. በአማራ እና በትግራይ ክልሎች መካከል አከራካሪ በሚባሉ የምርጫ ክልሎች ላይ በሰጠው ውሳኔ ላይ ተመስርቶ ነው። ቦርዱ የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም የዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ ባቀረበው የእግድ አቤቱታ መነሻነት፣ ፍርድ ቤቱ የቦርዱ ውሳኔ ለጊዜው ታግዶ እንዲቆይ ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወሳል።

የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት እና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ በጠበቃው ቴዎድሮስ ታደሰ አማካኝነት ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው አቤቱታ፣ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ መግባት ያስፈለገበትን ዋና ዋና ነጥቦች ዘርዝሯል።

የሁመራ እና የአድረመፅ የምርጫ ክልሎች ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ ከትግራይ ክልል ወጥተው በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ስር ራሳቸውን እያስተዳደሩ መሆናቸውን ገልጿል።

ኮሚቴው ላለፉት አሥር ዓመታት የሕዝብ ፒቲሽን (ፊርማ) በማሰባሰብ የሕዝቡን የማንነትና የወሰን ጥያቄ በሕጋዊ ውክልና ሲያስፈጽም የቆየ አካል መሆኑን ጠቅሷል።

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 38 የተደነገገው የመምረጥና የመመረጥ መብት በቀጥታ የሚነካ በመሆኑ፣ ኮሚቴው ባልተሳተፈበት የፍርድ ቤት ክርክር የሚሰጥ ማንኛውም ውሳኔ በሕዝቡ ላይ የጥቅም ጉዳት እንደሚያደርስ አመልክቷል።

ኮሚቴው በፍታብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 መሠረት በክርክሩ ውስጥ ገብቶ እንዲከራከር እንዲፈቀድለት የጠየቀ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱም ይህንኑ የጣልቃ ገብነት ጥያቄ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለየካቲት 25 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ይህ ክርክር አከራካሪ በሆኑት አካባቢዎች የሚካሄደውን ምርጫ እና የወደፊት የአስተዳደር መዋቅርን አስመልክቶ የሚሰጡ ውሳኔዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addisreporternews
ስልክ ቁጥር፡ +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ሳዋ የሰለጠኑት የኦብነግ አባል “አብዲሪዛክ ኤርትራ” የሶማሊያ አየር ኃይል አዛዥ መሆናቸው እያነጋገረ ነው፤

አዲስ ሪፖርተር - ጄኔራል አብዲሪዛክ መሀሙድ ሀጂ 'ቃሎምቢ’ በቅፅል...

አሜሪካ በኢራን ላይ መጠነ ሰፊ ወታደራዊ እርምጃ መጀመሯን ፕሬዝዳንት ትራምፕ አስታወቁ፤ የኢራን የጦር ተቋማት ይወድማሉ

ዋሽንግተን ዲሲ— የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የአሜሪካ ጦር...

“የትግራይ ሉዓላዊነት ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፤የትግራይ ሉዓላዊነት የሪፈረንደም ጉዳይ አይደለም” አቶ አማኑኤል አሰፋ

አዲስ ሪፖርተር - "የትግራይ ሉዓላዊነት ለድርድር የሚቀርብ አይደለም። የትግራይ...

Egypt’s Red Sea Signal: Opening the Door to a Historic Nile Agreement with Ethiopia

"sources like The National indicating Egypt's conditional openness to...