አዲስ ሪፖርተር – ለበርካታ ድምፃውያን የዜማና ግጥም ሰራዎችን አበርክተዋል፤ ትያትሮችን ጽፈዋል፤ አዘጋጅተዋል፡፡ የተሰፋዬ አበበ የኪነ ጥበብ ማዕከልን በመመስረት ስመጥር የኪነ ጥበብ ባለሙያወችን ያፈሩን ተሰፋዪ አበበ ተወልደው ለዚሁ ድንቅ ስራቸው የክብር ዶክተርነት ማዕረግ አግኝተዋል።
ላደጉበት ማኅበረሰብን በትምህርት ዘርፍ የመደገፍ ተግባራቸው በርክታ ስራዎችን አበርክተዋል። በዚህም ተግባራቸው በውል ይታወቃሉ። ለአብነት የማህበረሰብ ት/ቤቶች ግጥምና ዜማ በመድረስ ህብረ ዝማሬ ለማህበረሰቡ ማበርከታቸውን ስራቸውን የሚያውቁ ሁሉ ይመስክሩላቸዋል።
የአርቲስቱ ተግባር ትልቅ እውቀና የሚሰጠው እንደ ሆነ በመግለጽ የአብነት የማህበረሰብ ት/ቤቶች የቦርድ ሰብሰቢ ዶ/ር ዘላለም ተሾመ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ህብረ ዝማሬው በይፋ ሲመረቅ የተገኙት አርቲስት አብራር አብዶ እና ረ/ፕ ሙሉጌታ ጀዋሬ የአርቲሰቱን በጎ ተግባር በማድነቅ ለአርአያነታቸው ምሰጋና በአካል ስፍራው ላይ ሆነው አቀርበውላቸዋል፡፡
የማህበረሰብ ት/ቤቱ ለተሰፋዪ አበበ የአክሲዮን ድርሻ የቃል ኪዳን ሰነድ ያስረከበ ሲሆን የህይወት ዘመን ድጋፍ ለማድረግም ቃል ገብቷል። የክብር ዶክተርነት ማዕረግ የተሰጣቸው ተስፋዬ አበበ ለተደረገላቸው አመስግነዋል።







