አዲስ ሪፖርተር – በሀገራቸው ረሃብ እና ሰላም እጦት ቢበረታባቸው የተሻለ ህይወትን ፍለጋ ወደ አሜሪካ የተሰደዱ የዘር ሀረጋቸው ከምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሶማልያ የሚመዘዝ ስደተኞች ላይ የአሜሪካ መንግስት ብትር ጠንከር ብሎ መሰንዘር ጀምሯል።
እ.ኤ.አ. በዲሴምበር 15 2025 ሲቢኤስ ዜና ሚኒሶታ እንደዘገበው የሚኒፖሊስ እና የኢሚግሬሽን ወኪሎች (ICE) የሶማሌ ማህበረሰብ ማእከል በሆነው በካርሜል ሞል ዙርያ ኦፕሬሽን አካሂደዋል። በርካታ ግለሰቦችንም በቁጥጥር ስር በማዋል እና በማሰር በአካባቢው በሚገኙ ሶማሌዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የፍርሀት ድባብ ፈጥረዋል።
አዲስ ሪፖርተር ከዚህ ቀደም እንደዘገበችው በሚኒሶታ የሚገኝ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ድርጊት ለሕዝባዊ አገልግሎት የተመደበን በቢሊዮን የሚቆጠር የግብር ከፋዮች ገንዘብ በመደበኛ ባልሆነ የገንዘብ ዝውውር አማካኝነት ወደ አልሸባብ እጅ እንዲገባ ማድረጉን አመልክቷል። ይህ ድርጊት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በምስራቅ አፍሪካ ተወላጆች ላይ ጠንከር ያለ የቪዛ ማዕቀብ እና የማባረር እርምጃ እንዲዝቱ መነሻ ሆኗቸዋል።
ከዚህ አፈሳ እና ግጭትን በስተጀርባ ያለው መንስኤ እጅግ ብዙ የሶማሊያ ተወላጆችን ያካተተው እና ለአሸባሪው አል-ሸባብ የጀርባ አጥንት የሆነው የቢሊዮን ዶላሮች ዘረፋ ነው።
ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ተራምፕ በጉዳዩ ላይ በሰጡት መግለጫ ሶማሊያዎችን ‘ሀገራቸው መጥፎ የሆነችው በምክኒያት ነው ምክኒያቱም እነርሱ ቆሻሾች ናቸው’ በማለት ገልፀዋቸዋል።
ከሀገሩ የወጣ ካገሩ እስኪመለስ ቢጭኑት አህያ ቢጋልቡት ፈረስ ነውና ነገሩ ሶማሊያ ዎችም የሚደርስባቸውን ክብረነክ ስድብና ድርጊት ተቋቁመው በረሃብና በፍርሃት በራቸውን ቆልፈው መቀመጥ ምርጫቸው አድርገዋል።
ነዋሪዎች እንደሚናገረኡት በአንድ ወቅት እንደ ሴዳር-ሪቨርሳይድ እና ካርሜል ሞል ባሉ ሬስቶራንቶች እና የገበያ ኮሪደሮች ይታይ የነበረው ጫጫታ እና ሳቅ በፍርሀት እና በአርምሞ ተቀይሯል።
ኤምፒአር ዜና እንደዘገበው ጥቃቱን ተከትሎ ብዙዎቹ የአእምሮ ህክምና ደጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አምናለሁ ያሉት በሚኒያፖሊስ የካፒቶል ካፌ ባለቤት የሆኑት ፋርሃን አህመድ “ለንግድ ስራዬ ብቻ ሳይሆን ቤተሰቦቻቸው እየደረሰባቸው ያለውን ፍርሃት ለሚመለከቱ ህጻናት ጭምር እጨነቃለሁ” ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል።
አጭበርባሪ የሶማሊያ ዲያፖራዎች እናት ሀገራቸውን እንደ ምስጥ እየበላ ለሚገነድስ አሸባሪ ቡድንን ማደራጀታቸው ሳያንስ ይባስ ዛሬ በሰላም ሀገር ህይወታቸውን አቃንተው ወገን ዘመዳቸውን ረድተው ለሚኖሩ ሶማሊያውያን ሳይቀር መዘዛቸው መትረፉ ዛሬም በምስራቅ አፍሪካ እና በኢትዮጵያ የእናት ሀገራቸውን ሞት ለማፋጠን ለሚታትሩ ትልቅ ማስተማሪያ እንደሚሆን ግልፅ ነው።
በሀገራቸው ረሃብ እና ሰላም እጦት ቢበረታባቸው የተሻለ ህይወትን ፍለጋ ወደ አሜሪካ የተሰደዱ የዘር ሀረጋቸው ከምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሶማልያ የሚመዘዝ ስደተኞች ላይ የአሜሪካ መንግስት ብትር ጠንከር ብሎ መሰንዘር ጀምሯል።
እ.ኤ.አ. በዲሴምበር 15 2025 ሲቢኤስ ዜና ሚኒሶታ እንደዘገበው የሚኒፖሊስ እና የኢሚግሬሽን ወኪሎች (ICE) የሶማሌ ማህበረሰብ ማእከል በሆነው በካርሜል ሞል ዙርያ ኦፕሬሽን አካሂደዋል። በርካታ ግለሰቦችንም በቁጥጥር ስር በማዋል እና በማሰር በአካባቢው በሚገኙ ሶማሌዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የፍርሀት ድባብ ፈጥረዋል።
አዲስ ሪፖርተር ከዚህ ቀደም እንደዘገበችው በሚኒሶታ የሚገኝ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ድርጊት ለሕዝባዊ አገልግሎት የተመደበን በቢሊዮን የሚቆጠር የግብር ከፋዮች ገንዘብ በመደበኛ ባልሆነ የገንዘብ ዝውውር አማካኝነት ወደ አልሸባብ እጅ እንዲገባ ማድረጉን አመልክቷል። ይህ ድርጊት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በምስራቅ አፍሪካ ተወላጆች ላይ ጠንከር ያለ የቪዛ ማዕቀብ እና የማባረር እርምጃ እንዲዝቱ መነሻ ሆኗቸዋል።
ከዚህ አፈሳ እና ግጭትን በስተጀርባ ያለው መንስኤ እጅግ ብዙ የሶማሊያ ተወላጆችን ያካተተው እና ለአሸባሪው አል-ሸባብ የጀርባ አጥንት የሆነው የቢሊዮን ዶላሮች ዘረፋ ነው።
ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ተራምፕ በጉዳዩ ላይ በሰጡት መግለጫ ሶማሊያዎችን ‘ሀገራቸው መጥፎ የሆነችው በምክኒያት ነው ምክኒያቱም እነርሱ ቆሻሾች ናቸው’ በማለት ገልፀዋቸዋል።
ከሀገሩ የወጣ ካገሩ እስኪመለስ ቢጭኑት አህያ ቢጋልቡት ፈረስ ነውና ነገሩ ሶማሊያ ዎችም የሚደርስባቸውን ክብረነክ ስድብና ድርጊት ተቋቁመው በረሃብና በፍርሃት በራቸውን ቆልፈው መቀመጥ ምርጫቸው አድርገዋል።
ነዋሪዎች እንደሚናገረኡት በአንድ ወቅት እንደ ሴዳር-ሪቨርሳይድ እና ካርሜል ሞል ባሉ ሬስቶራንቶች እና የገበያ ኮሪደሮች ይታይ የነበረው ጫጫታ እና ሳቅ በፍርሀት እና በአርምሞ ተቀይሯል።
ኤምፒአር ዜና እንደዘገበው ጥቃቱን ተከትሎ ብዙዎቹ የአእምሮ ህክምና ደጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አምናለሁ ያሉት በሚኒያፖሊስ የካፒቶል ካፌ ባለቤት የሆኑት ፋርሃን አህመድ “ለንግድ ስራዬ ብቻ ሳይሆን ቤተሰቦቻቸው እየደረሰባቸው ያለውን ፍርሃት ለሚመለከቱ ህጻናት ጭምር እጨነቃለሁ” ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል።
አጭበርባሪ የሶማሊያ ዲያፖራዎች እናት ሀገራቸውን እንደ ምስጥ እየበላ ለሚገነድስ አሸባሪ ቡድንን ማደራጀታቸው ሳያንስ ይባስ ዛሬ በሰላም ሀገር ህይወታቸውን አቃንተው ወገን ዘመዳቸውን ረድተው ለሚኖሩ ሶማሊያውያን ሳይቀር መዘዛቸው መትረፉ ዛሬም በምስራቅ አፍሪካ እና በኢትዮጵያ የእናት ሀገራቸውን ሞት ለማፋጠን ለሚታትሩ ትልቅ ማስተማሪያ እንደሚሆን ግልፅ ነው።
ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/addisreporternews/
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter11
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393






