አዲስ ሪፖተር – በሰሜን ምዕራብ ትግራይ አቅጣጫ ጦርነት መካሄዱ ተሰማ። በጦረንቱ የአርሚ አስራ አንድ ብርጌድ 113 ክፍለ ሰራዊት አዛዥና የሎጅስቲክ ኃላፊዎች መማረካቸውን ምስል አስደግፈው የአዲስ ሪፖርተር የስፍራው ተባባሪዎች አስታውቀዋል።
ወደ ተከዜ ለመሻገር ዕቅድ የነበረው ይህ ውጊያ የተጀመረው በጠለምት ማይ ዳጉሽ ሲሆን በስፍራው የነበረው የመከላከያ ኃይል በውሰደው እርምጃ ለጊዜው መቋጨቱ ታውቋል። በአካባቢው ሃራ መሬት ራሳቸውን የትግራይ የሰላም ኃይሎች ብለው የሚጠሩ ቢኖሩም በውጊያው ላይ ያላቸው ሚና አልተገለጸም።
በምስል ተደግፎ የደረሰን ዜና እንደሚያመልክተው እንደ ብሬል፣ ተቀጣጥይ ፈንጂዎች፣ የተለያዩ የነብስ ወከፍ መሳሪያዎችና የመገናኛ ሬዲዮኖች ተማርከዋል። በቁጥር ያልተገለጹ በውጊያው መሞታቸውንም በመስል ለማረጋገጥ ተችሏል።

ከሰዓት በሁዋላ ላይ የተጀመረው ውጊያ ከሰዓታት በሁዋላ የቆመ ሲሆን በተጠቀሰው አቅጣጫ ሰብሮ ተከዜን ለመሻገር የተነሳው የትህነግ ታጣቂ ገሚሱ በማፈግፈግ ወደ መጣበት አቅጣጫ መመለሱ ታውቋል። ለጊዜው ውጊያው እንደቆመ ለማረጋገጥ ተችሏል።
በተገባደደው ሳምንት “እናመሰግናለን ሽሬ፤ ሰሞኑን ምዕራብ እንሻገር” የሚሉ እናቶች፣ ወልቃይትን ያስመልሳል ለተባለለት ሚሊሻ ምርቃት ሲዘፍኑና የማበረታቻ ፌስቲቫል ሲያካሂዱ እንደነበር ከስፈአው የወጣ የቪዲዮ ምስል በማስደገፍ ይፋ ማድረጋችን የሚታወስ ነው።
ከሳምንት በፊት ጄኔራል ምግበይ “ነባሩን አስተዳደርና የጸጥታ ኃይሉን ትተው ተፈናቃዮችን ብቻ ሊወስዷቸው ነው፤ ስለዚህ በሚቀጥለው ሳምንት ወልቃይትን እናስመልሳለን” ማለታቸውን ስብሰባው ላይ የተገኙ ጠቅሰን መዘገባችን አይዘነጋም። በዚሁ ንግግራቸው ጄነራሉ ከኤርትራ አስፈላጊ መሳሪያዎች መገኘቱንና የከፋ ነገር ከተፈጠረ የኤርትራ ወታደሮች ጦርነቱ ላይ እንደሚሳተፉ አመልክተው ነበር።
ይህን ባሉ በቀናት ልዩነት ደግሞ በሱዳን የኤርትራ፣ የሱዳንና የትግራይ ሕዝብ አንድ ነው በሚል የጥምረት በዓል መከበሩን የትህነግ ደጋፊ ሚዲያዎች በሰበር ዜና አውጀው ነበር። በዚሁ ጥምረት ላይ የፋኖ መሪ መገኘታቸውም ይፋ ሆኗል።
ጦርነቱን አስመልክቶ በድልም ይሁን በሽንፈት ከትህነግ በኩል በይፋ የተባለ ነገር የለም። ከትህነግ መረጃ የሚያገኙና ሻዕቢያ የሚያንቀሳቅሳቸው የሚታወቁ ሚዲያዎች ይህ እስከተዘገበ ድረስ ያሉት ነገር የለም።
በጦነቱ ወቅት የደረሰውን ጉዳት ከማተም መታቀባችንን ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን። እማኞች ጦርነቱ ሲካሄድ መስማታቸውን ወዲያው መቆሙን ለተባባሪዎቻችን አስታውቀዋል። ዘወትር ተጨማሪ መረጃዎችን እየተከታተልን እናሳውቃለን።
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addisreporternews
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393






