አዲስ ሪፓርተር— በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል በፓኪስታን አስተናጋጅነት ሲካሄድ የነበረው ቀጥተኛ የሰላም ድርድር፣ ከዘጠኝ ሰዓታት በላይ ከፈጀ አድካሚ ውይይት በኋላ ያለ ምንም ስምምነት መጠናቀቁ ተገለጸ።
በዚህ ታሪካዊና ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበት ድርድር ላይ የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ጄ.ዲ ቫንስ (JD Vance) የተገኙ ሲሆን፣ በኢራን በኩል ደግሞ የሀገሪቱ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ባለስልጣናትና የአብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) ቁልፍ አመራሮች ተሳትፈዋል። ፓኪስታን ሁለቱ ተቀናቃኝ ሀገራት ወደ አንድ የጋራ ስምምነት እንዲመጡ ከፍተኛ ጥረት ብታደርግም፣ ውይይቱ ሳይሳካ ቀርቷል።
የውይይቱ አጀንዳዎች በዋናነት የሚከተሉትን ነጥቦች ያካተቱ ነበሩ፦ የደህንነት ዋስትና እና የኢኮኖሚ ጉዳዮች፣ የእስረኞች ልውውጥ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች፣ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ ክፍት ሆኖ እንዲቀጥል የሚያስችል ስምምነት ነበር።
ኢራን አሜሪካ ያቀረበቻቸውን ጥያቄዎች “ሚዛናዊ ያልሆኑና የተጋነኑ” (Maximalist) ስትል ውድቅ አድርጋለች። በዚህም ምክንያት በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነትም ሆነ በኒውክሌር ጉዳይ ላይ ምንም ዓይነት መሻሻል ሳይታይ ቀርቷል።
ሁለቱም ወገኖች ድርድሩን እሁድ ዕለት ለመቀጠል ቢቀጥሩም፣ የተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት ግን ለበርካታ አስርት ዓመታት “ሞት ለአሜሪካ” እያለ ከሚጮህና ሽብርተኝነትን ከሚደግፍ አገዛዝ ጋር መተማመን ምን ያህል ከባድ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ተብሏል።
ይህ የኢስላማባዱ ንግግር እ.ኤ.አ. ከ1979 በኋላ የታየ ትልቁ የፊት ለፊት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቢሆንም፣ የአሜሪካን ጥቅም እና ወዳጆችን በውክልና ጦርነት (Proxies) ከሚያጠቃ የሃይማኖታዊ አምባገነን መንግስት ጋር ስምምነት ላይ መድረስ ምን ያህል ፈታኝ እንደሆነ በተጨባጭ የታየበት ሆኗል።
አሜሪካ ጠንካራ አቋሟን መቀጠል እንዳለባት የሚገልጹ ወገኖች፣ “ከፍተኛ ግፊት” (Maximum Pressure) ቀደም ሲል ውጤታማ እንደነበርና አሁን የሚታይ ማንኛውም ድክመት ተጨማሪ ጥቃቶችን ሊጋብዝ እንደሚችል እያሳሰቡ ይገኛሉ።
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addisreporternews
ስልክ ቁጥር፡ +251116393393






