ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የአክሲዮን ዝውውሮች እንዲቆጣጠር ስልጣን የሚሰጠውን ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱን ተሰማ

Date:

አዲስ ሪፖርተር – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከባንኮች ከፍተኛ ባለአክስዮኖችን ከመቆጣጠር አንስቶ እሰከ ማገድ የሚያስችል ሰልጣን የሚሰጠው ረቂቅ መመርያ መሰናዳቱን የተገለፀ ሲኾን ረቂቅ መመርያው ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላትን ለመከታተል እንዲያስችለው የሚረዳ መኾኑን ተገልጿል።

ብሔራዊ ባንክ ያዘጋጀው ረቂቅ መመርያ በዋነኝነት ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላትና ግለሰቦች የገንዘባቸውን ምንጭ እንዲያሳውቁ የሚያስገድድ ስልጣን የሚሰጥ መኾኑንና የተገለፀ ሲኾን አጠቃላይ የፋይናንስ ዘርፉን ጤና ለመጠበቅ ያለመ ነው ተብሏል።

ባንኩ መመሪያውን ለማውጣት የተገደደበት ምክንያት ሲገልፅም በባንኮች ውስጥ የሚኖሩ የአክሲዮን ዝውውሮች ግልፅና ድርሻቸውን በዓለማቀፍ ደረጃ ያለውን የድርሻ መስፈርቶችን ባሟላ መልኩ መካሄዱን ለማረጋገጥና የባንክ ስራ የመጠበቅ ኃላፊነቱ እንዲወጣ የሚረዳው መኾኑን ገልጿል

በቀጣይም ረቂቅ መመሪያውን ለባለድርሻ አካላት እንዲወያዩበት ባንኩ ግብዣ እንደሚያደርግና አስተያየቶችን መስማት እንደሚፈልግ የተገለፀ ቢሆንም በተዘጋጀው በረቂቅ መምርያ ሐሳባቸውን እንዲሰጡ በሚጋበዙት አካላት ዙርያ ባንኩ ያለው ነገር የለም።

በመጀመሪያ ዙር ረቂቅ መመርያው ላይ የሚሰጡ ጠቃሚ አስተያየቶችን ተቀብሎ ለመመርያው ግብአትነት ለማዋል ዝግጁ መኾኑንና ረቂቅ መመርያው በቅርቡ በምክር ቤት የፀደቀው የባንክ ስራ አዋጅን አቅም የሚሰጡ ነጥቦች የተካተቱበት መኾኑንም ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል ።

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ሃገራዊ የወርቅ ገበያ ዋጋ መናሩ የተለያየ ትንተና እየቀርበበት ነው

አዲስ ሪፓርተር ጥቅምት 12 ቀን 2018 አዲስ አበባ -...

ኦርቶዶክስ በኢትዮጵያ የተለያየ የፓለቲካ ፍላጎት ያላቸው ወገኖች ችግሮቻቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበች

አዲስ ሪፖርተር ጥቅምት 2 ቀን 2018 በኢትዮጵያ እየተወሳሰበ የመጣውን...

“ኤርትራ እንደ አገር ትክሰማለች”

የአየር ንብረት ለውጥ አደጋና ስጋትን መቋቋም ከማይችሉት አገራት መካከል...