ኢዜማ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሚካሄድባቸው ሁሉም አካባቢዎች እንደሚወዳደር አስታወቀ

Date:

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ሁሉም አካባቢዎች እንደሚወዳደር አስታወቀ።

የኢዜማ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ኢዮብ መሳፍንት ፓርቲው ለ7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ እያደረገ ያለውን ዝግጅትን አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ ላይ እንዳሳወቁት ፓርቲው በምርጫው ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሕዝብን ድምጽ ለማግኘት ላለፉት አራት ዓመታት ሲዘጋጅ ቆይቷል።

ኢዜማ በሰላማዊ መንገድ ብቻ መንግሥት ለመሆን እንደሚሠራ የገለጹት ደግሞ የፓርቲው ሊቀመንበር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ (ዶ/ር) ናቸው።

መንግሥት ምርጫውን ነጻ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚጠበቅበትን እንዲወጣና ባለድርሻ አካላትም ምርጫው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ የድርሻቸው ኃላፊነት እንዲወጡ ኢዜማ ጥሪ አቅርቧል።

መራጩ ሕዝብም የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ እና ሀሳብን መዝኖ እንዲመርጥ፤ ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከስሜት ቀስቃሽ እንቅስቃሴ ታቅበው የመፍትሔ ሀሳብ በማቅረብ ዕድሉን በኃላፊነት እንዲጠቀሙ ፓርቲው መልዕክት አስተላልፏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም ምርጫውን ከፍ በሚያደርጉ ተግባራት ላይ አተኩሮ እንዲሠራ ኢዜማ መጠየቁን ኢዜአ ዘግቧል።

ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addisreporternews
ስልክ ቁጥር፡ +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ቴድሮስ ካሳሁን ለሰዋሰው መልቲሚዲያ 33 ሚሊዮን ብር ከፍሎ በሰላም ፍቺ ማደረጉ ይፋ ሆነ

"ቴድሮስ በማህበራዊ ገጹ እውነቱን ለምን አይናገርም? በስማ በለው በማህበራዊ...

በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል በፓኪስታን ሲካሄድ የነበረው ድርድር ያለ ስምምነት ተበተነ

አዲስ ሪፓርተር— በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል በፓኪስታን አስተናጋጅነት...

ሻዕቢያ ያደራጀው የአመጽ ቀስቃሽ ኮሚቴ ዲያስፖራው ስለፈራ አገር ቤት አመጽ ማስነሳት ቅድሚያው አደረገ

ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ፤ ኢህአፓን ማገዝና ብረት ያንሱ ድርጅቶችን...