ኃይሌ ገብረስላሴ “አረቄን እጠቀም ነበር” በማለቱ ዕግድ ተጣለበት፤ እግዱ ለዓለም ዓቀፍ ተቋማትና ማህበራት ተበትኗል

Date:

አዲስ ሪፖርተር – አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ አረቄን ከዶፒንግ ጋር አያይዞ በግልጽ በሚዲያ መናገሩን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የዕግድ ቅጣት ማስተላለፉንና በአትሌቱ ንግግር ሳቢያ ሊከሰቱ የሚችሉ አሉታዊ ጉዳዮችን የሚከታተል ኮሚቴ ማቋቋሙን አስታወቀ። ኃይለ ምላሽ ካለው በሚል በግል ስልኩ በተደጋጋሚ ቢደወልም ምላሽ አልሰጠም። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውሳኔውን ዘግይቶ ለሕዝብ ይፋ ያደርገበትን ምክንያት አስታውቋል።

ከስር ሊንኩ በተቀመጠው ዩቲዩብ ላይ ኃይሌ “ወርቅሻ” ካለው አትሌት ለውድድር ወደ ውጪ አገር አረቄ ይዘው እንደሚሄዱና እንደሚጠቀሙ ሲገልጽ ይሰማል። በንግግሩ “ጥንቃቄ” እንደሚያስፈልግ ገልጾ ቢናገርም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እሳቤው በራሱ አደጋ እንዳለውና ኃይሌ የመልካም ነገሮች ምሳሌ መሆን ሲገባው አረቄን በገሃድ ማስተዋወቁና ማበረታታቱን ነቅፏል። ስፖርትና የአልኮል መጠጥ እጅግ የተለያዩና በምንም አግባብ ሊዛመዱ እንደማይችሉ የተለያዩ የዓለም ዓቀፍ ህጎች ያዛሉ።

ከለውጡ በሁዋላ መንግስት በኢትዮጵያ የመጠጥ ማስታወቂያዎችን ሙሉ በሙሉ ማገዱ ካከናወናቸው ደግ ተግባራት መካከል የሚነገርለትና በሕዝብ ዘንዳ የተወደደለት እንደሆነ በወቅቱ በስፋት አስተያየቶች የተሰጠበት ጉዳይ ነበር። በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከሚዲያ ሰዎች ጋር በነበራቸው ውይይት ላይ አንዳንድ ሚዲያዎችች ” በገቢ ራሳችንን መቻል አቃተን፣ ቢሮ በአንድ ህንጻ ላይ ይሰጠን፣ የአልኮል መጠጦችን ማስታወቂያ እንድንሰራ ይፈቀድልን” በማለት መጠየቃቸው በስብሰባው የተካፈሉ በግል ሚዲያቸው ይፋ ሲያደርጉት ሰፊ መነጋገሪያ ሆኖ እንዳለፈ አይዘነጋም። ጠቅላይ ሚኒስትሩም “ይህን አታስቡት” በማለት ስለ ማህበራዊ ኃላፊነት በጥልቅ አስረድተው ጥያቄው ሁለተኛ እንዳይነሳ ማሳሰባቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እጅግ አምርሮ ኃይሌን በነቀፈበት መግለጫው አረቄንና ዶፒንግን ማገናኘት አደገኛ መሆኑን አትቷል።

የአልኮል መጠጥ በዓለም ዓቀፍ ጸረ ዶሚንግ ኤጀንሲ እንደማይደገፍ መግለጫው አንስቶ፣ ኃይሌ ይህን እያወቀ “አረቄን እንደ ዶፒንግ ትጠቀማለህ?” ለሚለው ጥያቄ የሰጠው መልስ በአገር ደረጃ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያስከትል አመልክቷል።

ኃይሌን የድል፣ የሪኮርድና የሀብት ተምሳሌት ያደረገው መግለጫው፣ ኃይሌ በዚሁ አርአያነቱ ከመቀጠል ይልቅ አረቄን ሲያበረታታ መታየቱ ወጣቱን ተውልድ፣ ተተኪ አትሌቶችንና ግንዛቤያቸው አነስተኛ የሆኑትን የሚያሳሳት እንደሆነ አመልክቷል።

በዚሁ መነሻ በአገር ውስጥና በውጭ ጉዳዩን የሚከታተሉ ሶስት አባላት ያሉት ኮሚቴ ማቋቋሙን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ይፋ አድርጓል። በመሆኑም ኃይሌ በተናገረው ጉዳይ ዙሪያ የሚደረጉ ማጣራቶች እስኪጠናቀቁ ድረስ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ኃይሌ ላይ ጊዜ ገደብ የሌለው ዕግድ አጽንቷል።

በውስኔው መሰረት ኃይሌ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ስም ተጠቅሞ ምንም ዓይነት ተግባር እንዳያከናውን ታግዷል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ስምን ተጠቅሞ ማናቸውን ማስታወቂያዎች ከሚታወቁ ስፖንሰር ሽፕ አድራጊዎች ጋር እንዳያከናውን መከለከሉን መግለጫው አመልክቷል። ለስፖንሰር ሺፕ አድራጊዎችም የውሳኔውን ቅጂ መላኩን አመልክቷል።

ዕግዱ በተለያዩ ቋንቋዎች ታዘጋጅቶ ለዓለም ዓቀፍ ተቋማት እንዲሰራጭ መታዘዙን መግለጫው አመልክቷል። ይህን ተከትሎ ኃይሌ ከአረቄ ጋር ተያይዞ የሰሞኑ አጀንዳ ይሆናል ተብሎ ተገምቷል። በ

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባለድርሻ አካላት በዚሁ ዙሪያ መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩና አረቄ ለስፖርተኞች እጅግ ጎጂ መሆኑን በመግለጽ ድርጊቱን እንዲያወግዙ አሳስቧል። ጥሪ አስተላልፏል።

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ኃይሌን ማገድ ስለመቻሉ የህግ ባለሙያ ጠይቀን “አዎ ይችላሉ፤ ጉዳዩ ለእኛ ቀላል ይመስላል። ለዓለም ዓቀፍ ተቋማት ከፍተኛ ትርጉም ያለው ጉዳይ ነው። የኃይሌንም ስምና የነበረውን ክብር ያጎድፈበታል፤ ዜናው በዓለም ዓቀፍ መድረክ መነጋገሪያ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም” ብለዋል።

ኃይሌ ከውጭ አገር ትጥቅ አምራቾች ጋር መጠኑ የማይታወቅ የስፖንሰር ሺፕ ውል እንዳለው ይታወቃል። ይህ ለረጅም ዓመታት የኖረ ውል በኦሊምፒክ ወይም በአትሌቲክስ ወይም በራሱ ስም የተፈጸም እንደሆነ ባይታወቅም፣ ኃይሌ በስፖንሰር ሺፕ ከፍተኛ ጥቅም ከሚያገኙ የዓለማችን ሯጮች መካከል አንዱ ነው። ከዚህ አንጻር መግለጫው ከአረቄ ጋር በተያያዘ ዕግድ እንደጣለ ማስታወቁ የትጥቅ አምራቾቹ ለስማቸው ሲሉ አቋም እንዲውሰዱ ሊያስገድዳቸው እንደሚችል ተገምቷል።

ኃይሌ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ስላሰራጨው መግለጫ ምላሽ እንዳለው ለማነጋገር በግል የእጅ ስልኩ ቢደወልለትም ምላሽ አልሰጠም። ምላሽ ሲሰጥ የሚስተናገድ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ቀደም ሲል ያወጣውን መግለጫ ለሕዝብ ይፋ ሳያደርግ የቆየበትን ምክንያት አስመልክቶ ለአዲስ ሪፖርተር እንዳለው ለኃይሌ ዕድል ለመስጠት ሲባል ነው።

“አስተያየት፣ ቅሬታ ወይም ውሳኔውን አስመልክቶ ምላሽ ካለው ዕድሉን እንዲያገኝ ሲባል ውሳኔው ተልኮለት ምላሽ እንዲሰጥ ዕድል መስጠቱ አስፈላጊና አግባብ በመሆኑ ምላሹ ሲጠበቅ ነበር” ያለው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ አትሌት ኃይሌ ምላሽ ባለመስጠቱ መግለጫው ዘግይቶ ይፋ እንደሆነ አመልክቷል።

ጉዳዩ በዘፈቀደ የሚነገሩ ንግግሮች በተለይም ከሚታወቁ ሰዎች ሲሆን የሚያስከትሉት አሉታዊና አዎንታዊ መልዕክት ከፍተኛ በመሆኑ ጥንቃቄ እንደሚያሻው፣ ይህም ለሌላ ጊዜ ትምህርት እንደሚሆን የህግ ባለሙያው ተናግረዋል። ኃይሌ በተለያዩ ጉዳዮች ያለ በቂ መረጃ አስተያየት በመስጠት በተደጋጋሚ የሚተች እንደሆነ ይታወቃል። “የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲ አያስፈልገውም” በማለት የሰጠው አስተያየትና በቅርቡ “እኔም እርቦኛል” በማለት መናገሩ በስፋት ካስወቀሱት የሚጠቀሱ ናቸው፤ ግብርን አስመልክቶ አንዴም “ጨዋ ግብር ከፋይ” ከሚባሉት ተርታ ስሙ አለመጠራቱ፣ ታላቁ ሩጫ “ትርፍ አልባ” ተብሎ በሚሰራበት ወቅት ከቀድሞ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች ጋር ድርጅቱ በውጭ አገር ባለው የውጭ አካውንትና በሚያገኘው ከፍተኛ ገቢ ሳቢያ ውዝግብ ውስጥ ገብቶ እልባት ሳይሰጠው የቆመ ጉዳይ እንደሆነ በወቅቱ ሪፖርተር ጋዜጣ መዘገቡ አይታወስም።

አዲስ ሪፖርተር ይህንና መስለ ጉዳዮችን፣ ታላቁ ሩጫ ከብሄራዊ ባንክ ሲወስድ ስለነበረው የውጭ ምናዛሬና የመወዳደሪያ ቲሸርት ከአገር ውስጥ ይገዛ እንደነበር ያላትን መረጃ አሰባስባ የድርጅቱን አስተያየት በማካተት የምርመራ ሪፖርት እንደሚያቀርብ ከወዲሁ ይፋ ያደርጋል። ሪፖርቱ ሲዝጋጅ የውድድሩን አገራዊ ፋይዳ ሳይነካ፣ ሲከተለ በነበረው አሰራር ዙሪያ ላይ ብቻ የሚያተኩር ይሆናል።

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ፕሬዝዳንት ትራምፕ አሜሪካን ከ66 ዓለም አቀፍ ተቋማት የሚያስወጣ ትዕዛዝ ፈረሙ

አዲስ ሪፓርተር - በዓለም ፖለቲካ ውስጥ እጅግ አስደንጋጭ የተባለ...

የመኖሪያ ቤት አብዮት? ዜጎች በገቢያቸው መጠን የቤት ባለቤት መሆን የሚያስችል ፖሊሲ ጸደቀ

አዲስ ሪፖርተር - አቅምን ያገናዘበ፣ ተደራሽና በዘላቂነት ሊቀርብ የሚችል...

ሀያላኑ ሀገራት በየራሳቸው የቤት ስራ ተጠምደዋል፤ በቬንዝዌላ ላይ የሩስያ እና አሜሪካ ስትራቴጂካዊ አላማ

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካው ወታደራዊ ዘመቻ እና በቬንዙዌላው ኒኮላስ...