“እስክንድ ነጋ አልታሰረም” እስክንድር “የሰላም ንግግር የጀመረው እሱ ነው” በሚል በዘመቻ ውግዘት እያስተናገደ ነው

Date:

አዲስ ሪፖርተር – እስክንድር ነጋ መታሰሩን በመግለጽ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች የሚጽፉትና የሚያሰራጩት ዜና ስህተት መሆኑ ተሰማ። ለጊዜው የት እንደሚገኙ ከመግለጽ ተቆጥበው ከስክንድር ጋር አብረው እንደሚሰሩ የተናገሩ ለአዲስ ሪፖርተር እንዳሉት እስክንድ ባለበት ስፍራ ላይ ነው።

በምሬ የሚመራው ኃይል እንዳሰረውና ወደ የትም መሄድ እንደማይችል ተገልጾ መረጃ የሚሰራጨው በሰላም ድርድር ተስማምቶ ሊገባ ይችላል ከሚል ፍርሃቻ እንደሆነም ገልጸዋል። ሰላምን አስመልክቶ አሁን ላይ የተደረሰ ነገር ስለመኖሩ ዝርዝር አልተናገሩም።

ዜናውን ይበልጥ ለማስጥራት እስክንድርን ማናጋገር የሚቻልበት አግባብ እንዳለ ተጠይቀው “ለጊዜው አይሆንም” ብለዋል።

በርካታ በውጭ አገር ያሉ የቀድሞ የእስክንድር ወዳጆችና ተከታዮች ጭምር ሰሞኑን “ከሃዲ” በሚል እየዘለፉት ይገኛሉ። ከትናንት ጀምሮ “ምሬ አስሮታል” የሚል መረጃ እያወጡ ነው!! “ሰበር ዜና” በማለት “አቶ እስክንድር ነጋ እነ መከታው ማሞ በሚመሩት ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ተብሎ በሚጠራው ኃይል ቁጥጥር ውስጥ መሆኑ ታወቀ” የሚል ዜና ካሰራጩት ቡድኖች ውጪ ዜናውን በድርጅት ደረጃ ወይም በሚታወቅ አካል ያረጋገጠ የለም።

“አቶ እስክድር ነጋ የበላይነት ሲደረግ በነበረው ድርድር መሰረት የተወሰኑ የአፋህድ ከፍተኛ አመራሮች ለአገዛዙ አምልጠው እጅ ሲሰጡ አቶ እስክንድር ነጋ ግን በእነ መከታው ማሞ በሚመሩት ኃይል የቁም እስር ላይ መሆኑ ታውቋል” የሚሉት ዜና አቅራቢዎች፣ በዛው ዜናቸው ላይ “እስክንድር ነጋ ማምለጥ በማይችልበት ደረጃ ላይ ነው ሲሉ ምንጮች ገልፀዋል” ሲሉ መታሰሩን ጥያቄ ውስጥ የሚከት መረጃ አክለዋል።

ለአዲስ ሪፖርተር መረጃ የሰጡት ሰው እንዳሉት ከሆነ የሚባለው ሁሉ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የሚወጡ የስጋት ዜናዎች እንጂ፣ እውነታ የላቸውም። አዲስ ሪፖርተር በኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃባ ከሚመሩት የፋኖ አካል ውስጥ ካሉት የመረጃ ምንጮች ለማረጋገጥ ሞክራ “መረጃ የለኝም” የሚል ምላሽ አግኝታለች፤ እነሱ “ተከበዋል” የሚባለውን ግን አፋቸውን ሞልተው አስተባብለዋል። የአገር መከላከያ ከከበባ እንዳስለቀቃቸው የመከላከያ ምንጮቻቸውን ጠቅሰው ስለዘገቡት እግረምነገዳቸውን ጠይቀናቸው “አሁን ባለንበት ቦታ ላይ አለን” ብ፤ለዋል።

ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/addisreporternews/
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter11
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

አዲስ ሪፖርተር - ኢራን በእስራኤልና በአሜሪካ የተከፈተባትን  ጦርነት ለመመከት...

በፊንቴክ ኢንቨስትመንት የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ታዋቂ አርቲስቶች እና ድርጅቶች ንብረት በፍርድ ቤት ታገደ

አዲስ ሪፖርተር - በፊንቴክ ኢንቨስትመንት አማካኝነት "መኪና እናስመጣላችኋለን" በሚል...

የመሬት ይርጋና የታሪካዊው ሰበር ውሳኔ

አዲስ ሪፖርተር - በኢትዮጵያ የንብረት ሕግ ታሪክ ውስጥ ለዘመናት...

የአማራ ባንክ “ባንክ ካፕቸር” – አማራ ባንክ በጥቂት ግለሰቦች አንገቱ ታንቋል፣ ሕልውናውም አደጋ ላይ ነው

አዲስ ሪፖርተር - በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ትልቅ ተስፋ...