አዲስ ሪፖርተር ዜና – ኮሚሽኑ ምርጫው “መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ያልተፈጸመበት” እና “የተለመዱ ዓለም አቀፍ የምርጫ መስፈርቶችን ባሟላ” ሁኔታ የተፈጸመ መሆኑንም አረጋግጩያለሁ ብሏል።
ኢሰመኮ ይህን የገለጸው፤ በምርጫው ዕለት ያደረገውን ክትትል የተመለከተ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 25፤ 2018 ይፋ ሲያደርግ ነው። ሪፖርቱ ለመገናኛ ብዙሃን ያቀረቡት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር አቶ ብርሃኑ አዴሎ ናቸው።
እርሳቸው የሚመሩት መንግስታዊ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን፤ የትላንቱን ምርጫ ከታዘቡ ተቋማት አንዱ ነው። ኮሚሽኑ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት እና በተቋቋመበት አዋጅ፤ በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ሀገራዊ እና አካባቢያዊ ምርጫዎች “በሰብአዊ መብቶችን መርሆዎች መሰረት መከናወናቸውን የመከታተል” ስልጣን ተሰጥቶታል።
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addm






