ኢትዮጵያ የቀጥታ የባህር ዳርቻ ባይኖራትም፣ በወታደራዊ አቅሟ እና የባህር ላይ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባላት ከፍተኛ ፍላጎት ምክንያት በቀይ ባህር ደህንነት ንግግሮች ውስጥ ማዕከላዊ አገር ሆና ትቀጥላለች። በዚህም ምክንያት ዋሽንግተን የአዲስ አበባን የባህር ላይ ፍላጎት ችላ የማለት እድሏ አነስተኛ ነው፤ ምክንያቱም ይህን ማድረግ ቀጣናዊ አለመረጋጋትን ሊያባብስ እንደሚችል ሊያም ካር ይናገራሉ። “ኢትዮጵያ የባህር በር እንደምትፈልግ ግልጽ አድርጋለች፣ እናም ይህንን በኃይል ለማድረግ መሞከር በቀይ ባህር ደህንነት ላይ ጎጂ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል። ስለዚህ አሜሪካ ስጋቱን ችላ ብላ ቀጣናዊ ውጥረትን ከመቀስቀስ ይልቅ ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር እነዚህን ጉዳዮች ለመፍታት እየሞከረች …. ህልውናውም ነው “
“የምናደርገው የሚገባቸውና አብዝተው የሚቃወሙን ጠላቶቻችን ናቸው” አቢይ አሕመድ የባህር ኃይል ሲያቋቁሙ ለተነሳው ተቃውሞ ከተናገሩት
አዲስ ሪፖርተር ዜና “ውሃው መሟሟቅ ጀምሯል” ይላል አፍሪካን ሪፖርት። ዘገባው ይህንን ሪፖርት የመረጠው የአሜሪካ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት ዳግም መታደሱን አስመልክቶ ላቀርበው ሰፊ ዘገባ ነው። ዘገባው ህወሃት መጣሉንም ያስታውቃል። ዲፕሎማቶች ረስተውታል ሲል የምዕራብ አገራት ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ መንግስት ጎን መቆማቸውን ማስረጃ እየጠቀሰ ያስረዳል። የቀይ ባህርና የሱዳን እንዲሁም የመላው ምስራቅ አፍሪቃን ጂኦፖለቲካ አንስቶ ኢትዮጵያ ዋናዋ አንከር መሆኗን ያስታውቃል።
አሜሪካ በቀይ ባህር አካባቢ ካለው አለመረጋጋት አንጻር ስትራቴጂካዊ ትስስሯን እያጠናከረች መሆኗን ያተተው አፍሪካን ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ የዚህ ስትራቲርጂክ ጥምረት ቀዳሚ ተመራጭ አገር መሆኗን መረጃና ማስረጃ አቅርቦ ይተነትናል።
በዋሽንግተን እና በአዲስ አበባ መካከል የተጀመረው አዲስ የሁለትዮሽ ምክክር፣ ምንም እንኳን በትግራይ፣ በሱዳን እና በቀይ ባህር ኮሪደር ላይ ያልተፈቱ ውጥረቶች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀንድ የደህንነት ዲፕሎማሲ ማዕከል አድርጓታል። ዘገባው ዝርዝሩን ባያትምም አሜሪካ የተጠቀሱትን ችግሮች ለመፍታት እየሰራች መሆኗን የተለያዩ ሪፖርቶች ያስረዳሉ።
አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ግንኙነታቸውን ወደ ነበረበት ለመመለስ (reset) እየተንቀሳቀሱ ናቸው የሚለው ዜና በተለያዩ አውዶች መሰማት ከተጀመረ ቢከራርምም፣ ሰሞኑን ይፋ የሆነው ዜና ዋሽንግተን በአፍሪካ ቀንድ እየተበላሸ ባለው የደህንነት ሁኔታ ውስጥ አዲስ አበባ ቁልፍ ተዋናይ መሆኗን በይፋ ያወጀ ነው።
እ.ኤ.አ. ግንቦት 11 በዋሽንግተን የተካሄደው ከፍተኛ ደረጃ ምክክር የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስን፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ኃላፊ ሬድዋን ሁሴንን እና የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አማካሪ ግርማ ብሩን ከዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር አገናኝቷል። ከእነዚህም ባለስልጣናት መካከል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት ረዳት አሊሰን ሁከር እና ሌሎች በየደረጃው ያሉ ከፍተኛ ኃላፊዎች ይገኙበታል። ይፋ ባይወጣም፣ ከደህንነትና ከጸጥታ አንጻር ባገር ውስጥና በቀጠናው ስላለው የውክልና ጦርነት በስፋት ውይይት ተደርጓል። ኢትዮጵያም ያቀረበችው አሜሪካ መመለስ ያለባት ጥያቄዎች አሉ።
ስብሰባው በመከላከያ እና በመረጃ ትብብር፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት እንዲሁም ከሱዳን እስከ ቀይ ባህር ባለው ቀጣናዊ የደህንነት ቅንጅት ላይ ያተኮረ ነበር። ይህም ከትግራይ ጦርነት ጋር ተያይዞ ከዓመታት ውጥረት በኋላ ግንኙነቱን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለመመለስ በአሜሪካ በኩል የተደረገ ትልቁ ጥረትና ውሳኔ እንደሆነ አፍሪካን ሪፖርት አመልክቷል።
ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ የሆኑ የቀድሞ የህወሃት ጄኔራል፣ ዜናው ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ መሆኑን አመልክተው በትግራይ አቅጣጫ ጦርነት ሊከፈት እንደማይችል፣ ከሆነም ከተራ ግጭት እንደማያልፍ አመልክተዋል። ግጭት ሊነሳ የሚችለውም በህወሃት ውስጥ አሻግሮ የሚመለከት አመራር ባለመኖሩ፣ ሩጫው ሁሉ ለስልጣንና ስልጣንን ተመክቶ በወንጀል ላለመጠየቅ የሚደረግ ጫና መፍጠሪያ ስለሆነ ብቻ መሆኑንንም አመልክተዋል።
በአሜሪካን ኢንተርፕራይዝ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ተንታኝ የሆኑት ሊያም ካር፣ ይህ ሂደት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን ሚና እና የአሜሪካን ስጋቶች እውቅና መስጠት ነው ይላሉ። “እንደ ሱዳን እና ቀይ ባህር ያሉ አንገብጋቢ ጉዳዮች እንዲፈቱ እና በአፍሪካ ቀንድ ውስጥ ሰላም እንዲሰፍን አሜሪካ ፍላጎት አላት። በእነዚህ ጉዳዮች ውስጥ በሁሉም አግባብ ኢትዮጵያ ሚና አላት” ብለዋል።
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ አሜሪካ መገኘት ለውይይቶቹ የተሰጠውን ስትራቴጂካዊ ክብደት ይህንኑ እንደሚያሳይ ካር ተናግረዋ። “ይህ ተራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ብቻ አልነበረም፤ የኢትዮጵያ የመረጃ ኃላፊ እና የአብይ የቅርብ የደህንነት አማካሪ የሆኑት ሬድዋን ሁሴን፣ በሽብርተኝነት መከላከል፣ በቀይ ባህር የባህር ላይ ደህንነት፣ በቀጣናዊ ሽምግልና እና በመረጃ ቅንጅት ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል” ብለዋል።
ማርኮ ሩቢዮ በኤክስ ገጻቸው “ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ግጭቶችን በማርገብ እና በመላው ምስራቅ አፍሪካ መረጋጋትን በመደገፍ ረገድ ወሳኝ ሚና ትጫወታለች” ብለዋል። የአሜሪካ ባለስልጣናት በቀጣይነት በቀይ ባህር ላይ በሁቲዎች በሚፈጸሙ ጥቃቶች እና በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት እየተከሰተ ባለው የባህር ላይ ደህንነት እና የንግድ መስመሮች ስጋት ላይ ያላቸውን ስጋትም አንስተዋል።
እንደ ሊያም ካር ገለጻ፣ እነዚህ ፍላጎቶች ከጸረ-ሽብር ትብብር እና ከሱዳን ሽምግልና ጀምሮ እስከ አባይ ዲፕሎማሲ እና በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በቦይንግ መካከል ያለውን የንግድ ሽርክና ያካትታሉ።
አሜሪካ የወደብ ስጋቶችን እየፈታች ነው?
ኢትዮጵያ የቀጥታ የባህር ዳርቻ ባይኖራትም፣ በወታደራዊ አቅሟ እና የባህር ላይ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባላት ከፍተኛ ፍላጎት ምክንያት በቀይ ባህር ደህንነት ንግግሮች ውስጥ ማዕከላዊ ሆና ትቀጥላለች። በዚህም ምክንያት ዋሽንግተን የአዲስ አበባን የባህር ላይ ፍላጎት ችላ የማለት እድሏ አነስተኛ ነው፤ ምክንያቱም ይህን ማድረግ ቀጣናዊ አለመረጋጋትን ሊያባብስ እንደሚችል ሊያም ካር ይናገራሉ። “ኢትዮጵያ የባህር በር እንደምትፈልግ ግልጽ አድርጋለች፣ እናም ይህንን በሃይል ለማድረግ መሞከር በቀይ ባህር ደህንነት ላይ ጎጂ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል” ይላሉ። አክለውም “ስለዚህ አሜሪካ ስጋቱን ችላ ብላ ቀጣናዊ ውጥረትን ከመቀስቀስ ይልቅ ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር እነዚህን ጉዳዮች ለመፍታት እየሞከረች ሊሆን ይችላል” ሲሉ የሚያውቁትን ተናግረዋል።
ሱዳን፣ ማክሮን እና ልዩነት ያላቸው የዲፕሎማሲ ስሌቶች
የታደሰው የአሜሪካ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት በምዕራባውያን የአፍሪካ ቀንድ የደህንነት መዋቅር ላይ ከሚያደርጉት ሰፊ ዳግም ግምገማ ጋር አብሮ የሚሄድ ነው። የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት አማኑኤል ማክሮንም በቀጣዮቹ ቀናት አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። ማክሮን ከጉዟቸው በፊት ለ “The Africa Report” እንደተናገሩት፣ ለሱዳን ፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ድጋፍ በመስጠት ረገድ ዋሽንግተን የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን ብቻ የምትለይበትን መንገድ ከመከተል ተቆጥበዋል። ይልቁንም “ቡርሃንን (የሱዳን ጦር መሪ) የሚረዱትንም ጭምር” በማለት ምርመራው እንዲሰፋ ጠይቀዋል።
ይህ የሚያሳየው የሱዳን ጦርነት ወደ ቀጣናዊ ኃይሎች የውክልና ጦርነት መቀየሩን በምዕራባውያን ዘንድ እየታወቀ መምጣቱን ነው። የጂኦፖለቲካ ተንታኙ ይትባረክ ባለምላይ ከበደ እንደሚሉት፣ “ሳዑዲ አረቢያ እና ግብፅ የሱዳን ጦርን ሲደግፉ፣ ኤምሬትስ እና ኢትዮጵያ ደግሞ አር.ኤስ.ኤፍን (RSF) ይደግፋሉ፤ ሁለቱም የምዕራባውያን ወዳጆች ናቸው። ስለዚህ ጦርነቱን ለማቆም ሁለቱም ወገኖች ሁኔታውን እንዳያባብሱ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል” ብለዋል።
የትግራይ ውጥረት ከምዕራባውያን ቅድሚያ ዝርዝር ውስጥ እየጠፋ ነው?
የአሚሪካና የኢትዮጵያ አዲሱ ዲፕሎማሲያዊ ጥምረት፣ ምዕራባውያን ኃይሎች ከኢትዮጵያ ጋር ስትራቴጂካዊ ግንኙነታቸውን ለመገንባት እያደረጉ ያለው ጥረትሲ በትግራይ ያለውን ያልተፈታ ውጥረት ወደ ጎን እያሉት ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አስነስቷል። በትግራይ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ክልላዊ ምክር ቤት ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን የክልል ፕሬዝዳንት አድርጎ መሾሙ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መፍረስ እያበሰረ ቢሆንም የዓለም አቀፍ ተቋማትና የታላላቅ አገራት ምላ በጣም የቀዘቀዘ ነው። ይህም ህወሃት በዲፕሎማሲው አግባብ መጣሉን የሚያሳይ ነው።
ለአዲስ ሪፖርተር አስተያየት የሰጡት ጄኔራሉ፣ “ህወሃት አሁን ላይ ከሕዝብ ተነጥሏ። አቅም የለውም። የፖለቲካ እሳቤው አርጅቷል። ከምንም በላይ ህዝብ ሊያስተባብር የሚችልበት ምክኛት የለውም። ህዝብም ሆነ ልሂቃን አሁን ላይ ጦርነት አይፈልጉም። ሁሉም ነገር በህገ መንግስቱና በፕሪቶሪያው ስምምነት አግባብ እንዲከናወን ነው የሚፈልጉት” ሲሉ አሁን ላይ የሚታየው የዓለም ዝምታ የሚጠበቀ እነደሆነ አመልክተዋል። በቅርቡ ከትግራይ የዲያስፖራ አባላት ጋር ውይይት ያደረጉት ዶክተር አዲስ ዓለም ቤሌማም ይህንኑ ማረጋገጣቸው የሚታወስ ነው። በዚህም ሳቢያ በውጭ አገር ያሉ የክልሉ ተወላጆች እንደቀድሞ ተባብረው፣ በያሉበት አገራት ድምጻቸውን እንዲያሰሙና ጫና እንዲፈጥሩ ተማጽነው ነበር። ይሁን እንጂ ምላሹ ዝምታ ሆኗል።
ሊያም ካር እንደሚሉት፣ “ሀገራት አዲስ አበባን ከጎናቸው ለማሰለፍ እና እንደ ቀይ ባህር ያሉ ሌሎች ጉዳዮችን ለመፍታት ሲሉ ጠንካራ ምላሽ ከመስጠት ሊቆጠቡ ይችላሉ” በማለት ለህወሃት ጉዳይ ጀርባቸውን እንደሚሰጡ የአፍሪካን ሪፖርት ዘገባ ያስረዳል።
የህዳሴ ግድብ ዲፕሎማሲ እና ስትራቴጂካዊ ራስን መቻል
ምክክሩ ሌላውን ያልተፈታ የጂኦፖለቲካ ጉዳይ ማለትም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይን አንስቷል። ትራምፕ ቀደም ሲል ከኝዛቤ ጉድለት ግድቡ ወደ ግብፅ የሚፈሰውን ውሃ “ሊያቆም ይችላል” በማለት ተናግረው ነበር፣ አሁን ደግሞ በአዲስ አበባ እና በካይሮ መካከል ያለውን የሽምግልና ጥረት ለመጀመር ፍላጎት አላቸው።
ለኢትዮጵያ ባለስልጣናት ግን ግድቡ ከሉዓላዊነት እና ከስትራቴጂካዊ ራስን መቻል ጋር የተያያዘ ነው። ኢትዮጵያ ቀደም ሲል በነበሩት የአባይ ድርድር ውይይቶች ወቅት ያጋጠማትን የዲፕሎማሲ ጫና ሳታስተናግድ አዲስ የደህንነት እና የኢኮኖሚ ትብብር ትፈልጋለች። በተመሳሳይ ጊዜ፣ የምዕራባውያን ዋና ከተሞች አዲስ አበባ በቀጣናዊ መረጋጋት ጥረቶች ውስጥ ማዕከላዊ ሆና እስካለች ድረስ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ያልተፈቱ የውስጥ ውጥረቶችን ለመታገስ ፈቃደኛ የሆኑ ይመስላሉ።
ይትባረክ ባለምላይ “ኢትዮጵያ ለምዕራባውያን የምትረዳው በቀጣናዊ መረጋጋት ብቻ ሳይሆን አውሮፓን እያስቸገረ ያለውን የስደት ቀውስ ለመቆጣጠርም ጭምር ነው” ብለዋል። “የጂኦፖለቲካዊ አቀማመጧ እና ከፍተኛ የህዝብ ቁጥሯ በምዕራባውያን ኃይሎች እንድትመረጥ ትልቅ ሚና አለው” ሲሉ አክለው ማብራሪያቸውን ጨርሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገና ወደ ስልጣን ሲመጡ የኢትዮጵያን ባህር ኃይ፤ ዳግም በማቋቋም፣ አየር ኃይሉን በማዝመን ዘመናዊ የመከላከያ አቅም መገንባት እንደሚያስከብር፣ ተመራጭ እንደሚያደርግ ተናግረው ነበር። በወቅቱ “ባህር ሳይኖር ባህር ኃይል” በሚል ለሚተቹ “እኛ የምናደርገው የሚገባቸው ጠላቶቻችን ናቸው” በማለት ጥቅል ምላሽ ሰጥተው እንደነበር አይዘነጋም። በቅርቡ የባህር በር ጉዳይ ሲነሳ ደግም “ለአጀንዳ ማስቀየሪያ” በሚል ተቃውሞ ቢነሳም አሁን ላይ የሚሰሙ ዜናዎች አውዶቻቸው ፍጹም ሌላ ነው።
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addm






