የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በሰባት ውሃማ ስፍራዎች የውሃ ትራንስፖርት አገልግሎት ይጀመራል

Date:

አዲስ ሪፖርተር – የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በዓባያ፣ ጫሞ፣ ጣና ሀይቅ፣ ባሮ ወንዝ፣ ተከዜና በጊቤ ሰባት ውሃማ ስፍራዎች ላይ የውሃ ትራንስፖርት አገልግሎት ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ትግበራ በቅርቡ እንደሚገባ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ለአዲስ ሪፖርተር አስታውቋል።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የማሪታይም ባለሥልጣን የሎጀስቲክና ትራንስፎርሜሽን ቢሮ ዳይሬክተር ወርቁ ለማ ለአዲስ ሪፖርተር እንደገለጹት፤ በአስር ዓመት የትራንስፖርት ዘርፍ መሪ የልማት ዕቅድ የውሃ ትራንስፖርት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።

“የውሃ ትራንስፖርት ደህንነቱ የተጠበቀና በሚፈለገው ደረጃ በሀገራችን ያለውን ለውሃ ትራንስፖርት አገልግሎት አመቺ የሆኑ ወንዞችና ሐይቆች በአግባቡ በመጠቀም፤ ለሕዝብና ለጭነት ትራንስፖርት አመቺ ሆነው ይገኛሉ” ብለዋል።

የውሃ ትራንስፖርት አማራጭ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ሆኖ እንዲያገለግል እንዲሁም፤ ለመዝናኛና ለቱሪስት መስህብነትም እንዲያገለግሉ ሀይቆቹ መሰረተ ልማቶች በስፋት እንደተሟላላቸውም አብራርተዋል።

ለዚህም ማሳያ እንዲሆን ለጣና የውሃ ትራንስፖርት እንዲያገለግሉ ከተገዙት ሁለት ዘመናዊ ጀልባዎች መካከል፤ ሁለተኛዋ ጣናነሽ ሁለት ጀልባ ከቀናት በፊት ወደ ሀገር ቤት መግባቷን አስታውሰዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በዘርፉ የሚገኘው ገቢ በአግባቡ በመጠቀም የሀገር እድገትን ለማሳደግ ሰፋፊ ሥራዎች በመሰራት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

ካለው የሐይቆች ሀብት አንጻር እየተገኘ ያለው ገቢ ተመጋጋቢ እንዳልሆነ የገለጹም ሲሆን፤ በተለያዩ ምክንያቶች መገኘት የነበረበት ጥቅም አለመገኘቱን አያይዘው አንስተዋል።

ዳይሬክተሩ አያይዘውም፤ በሰለጠኑ ሀገራት የውሃ ላይ ትራንስፖርት በላቀ ደረጃ እንደሚገኝ አንስተው፤ ለሀገራቱ የቱሪዝም መዳረሻ ከመሆን ባሻገር የስፖርታዊ ውድድሮች የሚካሄዱበት ተጨማሪ ገቢ እንደሆነ ገልጸዋል።

ይህንኑ ልምድ በመቅሰም እንደ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ቅድመ ሥራዎች ተጠናቀው፤ በሀገሪቱ የሚገኙ ሀይቆች ለአገልግሎት አመቺ ተደርገው እንደተቀመጡ አብራርተዋል።

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

አሜሪካና ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ ምን እያሰቡ ነው? “አሜሪካ የኢትዮጵያን የባህር ፍላጎት ማሳካት ህልውናዋ ነው”

ኢትዮጵያ የቀጥታ የባህር ዳርቻ ባይኖራትም፣ በወታደራዊ አቅሟ እና የባህር...

“የአሜሪካና ኢትዮጵያ ወዳጅነት አደገኛ ነው፤ ከማን ጋር እንደምንዋጋ አልገባንም፤አሳልፋ ልትሰጠን ትችላለች”

አዲስ ሪፖርተር - በአገር ቤት ሕዝባዊ አመጽ ለማነሳሳት የተደራጀው...

ኤርትራ ለህወሃት መሪዎች የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት የመስጠት ስምምነት አገደች

አዲስ ሪፖርተር - የኤርትራ መንግስት ለህወሃት አመራሮችና ከፈተኛ ወታደራዊ...