የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

Date:

አዲስ ሪፖርተር ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት” መሆኑን ጽህፈት ቤታቸው አስታወቀ። ምርመራው ቀጥሎ ማስተባበያው ሃሰት ከሆን የከፋ ቀጣት ይጠበቃቸዋል።

ባለፉት ጥቂት ወራት የወጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ የኢልሀን ኦማር እና የባለቤታቸው ቲም ማይኔት ሀብት ከ51,000 ዶላር ወደ 30 ሚሊዮን ዶላር በድንገት ማደጉን ያሳዩ ነበር።

ይህ የ3,500 በመቶ ጭማሪ በሪፐብሊካን ፓርቲ አባላት እና በተለያዩ ተቋማት ዘንድ “ይህ ገንዘብ ከየት መጣ?” የሚል ጥያቄና ምርመራ አስነሳ።

በዚህ ሳምንት ሚያዝያ 21/2026 የኢልሀን ኦማር ጽህፈት ቤት በሰጠው መግለጫ፣ ቀደም ሲል የቀረበው ሰነድ የተሳሳተ መሆኑን አስታወቀ። እንደ መግለጫው ከሆነ፦
የስህተቱ አይነት፦የባለቤታቸው ኩባንያዎች ያላቸውን ጠቅላላ ንብረት እንጂ ያለባቸውን ዕዳ (liabilities) ሳይቀንስ በመመዝገቡ የመጣው ስህተት ሀአብታቸውን ከ30 ሚሊዮን በላይ አደረገው።

ጩኸቱ ከበረከተ በኃላ አሁን በተስተካከለው መረጃ መሠረት፣ የኢልሀን ኦማር እና የባለቤታቸው አጠቃላይ ሀብት በ18,004 እና በ 95,000 ዶላር መካከል ብቻ መሆኑ ተገልጿል።

የጽህፈት ቤቱ ቃል አቀባይ “ኢለሃን ሚሊየነር አይደለችም፤ እንዲያውም እስካሁን ያልተከፈለ የተማሪ ብድር አለባት” በማለት ወሬውን ለማስተባበል ሞክረዋል።

ምንም እንኳን የኢልሀን ኦማር ወገን “ስህተቱ ታርሟል” ቢልም፣ የሪፐብሊካን ፓርቲ መሪዎች ግን “30 ሚሊዮን ዶላር እንዴት በስህተት ይመዘገባል?” በሚል ጥርጣሬያቸውን እየገለጹ ነው። የምክር ቤቱ የቁጥጥር ኮሚቴ (House Oversight Committee) ጉዳዩን በጥልቀት መመርመሩን እንደሚቀጥል ይጠበቃል።

ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addm

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

ስዊድን ከአደገኛ ቡድኖችna ታጣቂዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ስደተኞች የመኖሪያ ፈቃድ የሚያሳጣ ሕግ ሥራ ላይ አዋለች

ከታጣቂዎች፣ ከአክራሪ ድርጅቶች ወይም ከተደራጁ የወንጀል መረቦች (Gangs) ጋር...

ከእስራኤል ትልቁ የስለላ መረብ የተስወረው 911 ቀናት የሆኑት ዕግታ፤ ሃይማኖት ካሳን ማን ሰወራት?

አዲስ ሪፖርተር፣ አዲስ አበባ — የአንድ ህፃን ልጅ በድንገት...

“ጦርነት ከተጀመረ ጦርነት የሰለቻቸው የህወሃት ኃይሎች ሙሉ በሙሉ ይፈርሳሉ፤ አመራሮቹም ይህን ያውቃሉ”

አዲስ ሪፖርተር፣ አዲስ አበባ — የሕወሓት ሰራዊት አዛዦች ከፌዴራል...

“አዲስ አበባን ኦሮሞ ዘረፋት? እውነቱን ልንገራችሁ” ተሳታፊ አባል The Truth About Addis Ababa: A National Dialogue Panelist’s

የቀረበውን ጽሑፍ ይዘትና መልእክት ሳይለወጥ፣ የፊደልና የሰዋሰው ግድፈቶች (ስፔሊንግ፣...