ታይለር ፔሪ የ 77 ሚሊዮን ዶላር የጾታዊ ጥቃት ክስ ተመሰረተበት

Date:

ከኢትዮጵያዊቷ ሞዴል ገሊላ በቀለ ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት የነበረውና የአንድ ልጅ አባት የሆነው ታዋቂው የሆሊውድ ፊልም አዘጋጅ ታይለር ፔሪ፣ ለሁለተኛ ጊዜ በጾታዊ ጥቃት የፍትሐ ብሔር ክስ እንደቀረበበት ‘ዘ ራፕ’ (TheWrap) ዘግቧል።

ክሱ የቀረበው እ.ኤ.አ Dec 26 ቀን 2025 ሲሆን ከሳሹ በ2016 “Boo! A Madea Halloween” በተሰኘው የፔሪ ፊልም ላይ የተሳተፈው ተዋናይ እና ሞዴል ማሪዮ ሮድሪጌዝ ነው።

 ሮድሪጌዝ “ታይለር ፔሪ በተደጋጋሚ ያልተገቡ የጾታ ጥያቄዎችን አቅርቦብኛል እንዲሁም የሥራ አካባቢውን አስቸጋሪ አድርጎታል” በሚል ቢያንስ 77 ሚሊዮን ዶላር የካሳ ክፍያ እየጠየቀ ይገኛል።

የክስ ማመልከቻው እንደሚለው ፔሪ በሆሊውድ ያለውን ተፅዕኖ ተጠቅሞ በሮድሪጌዝ ላይ ጫና አሳድሯል፤ እንዲሁም ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ ገንዘብ እንደሰጠው ተገልጿል።

ክሱ የፊልሙ አከፋፋይ የሆነው ‘ላዮንስጌት’ (Lionsgate) ተገቢውን ክትትል ባለማድረጉ በተባባሪነት ከሷል።

ይህ በ2025 (እ.ኤ.አ) ውስጥ በታይለር ፔሪ ላይ የቀረበ ሁለተኛው ትልቅ ክስ ነው።

ቀደም ሲል በሰባተኛው ወር ተዋናይ ዴሬክ ዲክሰን “The Oval” በተሰኘው የቴሌቪዥን ድራማ ላይ ሲሰራ የጾታ ትንኮሳ እንደደረሰበት በመግለጽ ክስ መስርቶ ነበር።

የፔሪ የሕግ አማካሪዎች ግን ክሱ መሰረተ ቢስ እና ለገንዘብ ተብሎ የቀረበ ነው በማለት የቀረቡትን ክሶች በሙሉ አስተባብለዋል።

ፌስቡክ፡ https://web.facebook.com/addisreporternews/
ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/addisreporter
ስልክ ቁጥር፡ +251981866434 / +251116393393

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

አሜሪካና ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ ምን እያሰቡ ነው? “አሜሪካ የኢትዮጵያን የባህር ፍላጎት ማሳካት ህልውናዋ ነው”

ኢትዮጵያ የቀጥታ የባህር ዳርቻ ባይኖራትም፣ በወታደራዊ አቅሟ እና የባህር...

“የአሜሪካና ኢትዮጵያ ወዳጅነት አደገኛ ነው፤ ከማን ጋር እንደምንዋጋ አልገባንም፤አሳልፋ ልትሰጠን ትችላለች”

አዲስ ሪፖርተር - በአገር ቤት ሕዝባዊ አመጽ ለማነሳሳት የተደራጀው...

ኤርትራ ለህወሃት መሪዎች የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት የመስጠት ስምምነት አገደች

አዲስ ሪፖርተር - የኤርትራ መንግስት ለህወሃት አመራሮችና ከፈተኛ ወታደራዊ...