የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ረቂቅ በጀት አጸደቀ

Date:

አዲስ ሪፖርተር ዜና አዲስ አበባ — የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባው ለቀጣዩ ለ2019 በጀት ዓመት የሚውል ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ረቂቅ በጀት በሙሉ ድምፅ አጽድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።

ለቀጣዩ ዓመት የቀረበው አጠቃላይ የበጀት መጠን 2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን 268 ሚሊዮን 126 ሺሕ 738 (2,339,268,126,738) ብር ሲሆን፤ ይህ በጀት ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግሥታት ድጋፍ እንዲሁም ለዘላቂ የልማት ግቦች (SDGs) ማስፈጸሚያ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።

ይህ የ2019 ዓ.ም. ረቂቅ በጀት የፌደራል መንግሥት ለ2018 በጀት ዓመት መድቦት ከነበረው 1.93 ትሪሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር የ409.2 ቢሊዮን ብር (ወይም የ21.2 በመቶ) ብልጫ አሳይቷል። ካለፉት አራት ዓመታት አጠቃላይ የበጀት ጉዞ አንጻር ሲታይም የዘንድሮው በጀት በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል። የፌደራል መንግሥት በጀት ከ2015 ዓ.ም. (786.6 ቢሊዮን ብር) አንጻር ሲነጻጸር በአሁኑ ወቅት በሦስት ዕጥፍ ገደማ (297.4%) ዕድገት ማሳየቱን የኤኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፤ የ2019 ዓ.ም. የፌደራል መንግሥት በጀት የተዘጋጀው የ2018 በጀት ዓመት “የፕሮግራም በጀት አፈጻጸምን መነሻ በማድረግ” መሆኑን ገልጿል። ይህም አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮ እና ኃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም እና የመንግሥትን የፋይናንስ አቅም ያገናዘበ መሆኑ ተመልክቷል።

ምክር ቤቱ ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም. በሚኖረው የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቀፍ ላይ በሰፊው የተወያየ ሲሆን፤ “የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ካሉበት ተግዳሮቶች እየተላቀቀ እና የኢኮኖሚው መሠረቶችም እየተጠናከሩ መጥተዋል” ሲል አስታውቋል። ይህ የ2019 ዓ.ም. በጀትም በኢኮኖሚ ሪፎርሙ የተገኙ አበረታች ውጤቶችን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱ ተገልጿል።

ረቂቅ በጀቱ አሁን ባለው ይዘት ላይ ምክር ቤቱ አስፈላጊ ግብዓቶችን ካካተተበት በኋላ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመራ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ሳምንታት በፓርላማው ሰፊ ውይይት ተደርጎበት ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ዌብሳይት፡ https://addisreporter.com/
ኢሜል፡ info@addisreporter.com
ቴሌግራም፡ https://t.me/addisreporter2
X፡ https://x.com/amejuju?s=21
https://web.facebook.com/addm

Share and Enjoy !

Shares

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

Share post:

Subscribe

spot_imgspot_img

Popular

More like this
Related

የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አንደበት የቆለፈው የትራምፕ መመሪያ ተቃዋሚዎች ተስፋ አስቆርጧል፤ አሜሪካ ስለምርጫው ለምን ዝም አለች?

አሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ የአገሪቱ ዲፕሎማቶች በሌሎች አገራት...